የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በምዕራብ ጉጂ ዞን የተሻሻለውን የግብርና አሰራር የተገበሩ አርሶ አደሮች ምርታቸው መጨመሩን ተናገሩ

Jan 13, 2025

IDOPRESS

ቡሌ ሆራ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ጉጂ ዞን የተሻሻለውን የግብርና አሰራር የተገበሩ አርሶ አደሮች ምርታቸው ከቀደመው ጊዜ በተሻለ መልኩ መጨመሩን ገልጸዋል፡፡

ከዞኑ የመኸር አዝመራ እስካሁን ከ5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡ የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አመልክቷል፡፡


ከአርሶ አደሮቹ መካከል አቶ ደንቦቢ ሀንቆ፣ የአፈርና ውሀ ጥበቃ፣ የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴና ሌሎች የግብርና ፓኬጆችን በአግባቡ መጠቀማቸው ለምርት መጨመር እገዛ እንዳደረገላቸው ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም ምርቱን ለማሳደግ የተጠቀሙት የተፈጥሮ ማዳበሪያ ወጪ በመቀነስና የአፈር ለምነት በመጨመር ከሄክታር 32 ኩንታል የስንዴ ምርት አስገኝቶላቸዋል፡፡


ለተገኘው አመርቂ ውጤት ከማሳ ዝግጅት እስከ ምርት አሰባሰብ በግብርና ባለሙያዎች የተደረገላቸው ክትትልና ድጋፍም ትልቅ ድርሻ እንዳለው አስታውሰዋል፡፡


አቶ ጎዳና በዴሳ በበኩላቸው፣ ለዘንድሮ የመኸር አዝመራ የተጠቀሙት ሙሉ የግብርና ፓኬጅ ምርታቸውን ከጠበቁት በላይ እንዳሳደገላቸው ገልጸዋል፡፡

እስካሁን በኩታ ገጠም ካለሙት ሁለት ሄክታር መሬት ከ36 ኩንታል በላይ የጤፍ ምርት መሰብሰባቸውን አስታውቀዋል፡፡


አርሶ አደር ኤዶ ጎበና በበኩላቸው 3 ሄክታር መሬታቸውን የስንዴና ጤፍ ሰብሎችን እያፈራረቁ በማልማት አመታትን አሳልፈዋል፡፡

የግብርና ስራቸው የተሻሻለ አሰራርን ያልተከተለ በመሆኑ ውጤቱም ዝቅተኛ፤ ኑሯቸውም ከእጅ ወደ አፍ እንደሆነ ያስታውሳሉ።

በግብርና ባለሙያዎች ምክርና እገዛ ሙሉ የግብርና ፓኬጆችን በመጠቃማቸው ዘንድሮ ከአንድ ሄክታር 22 ኩንታል ጤፍ ማግኘታቸውን አውስተዋል።

የምዕራብ ጉጂ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ አያኖ አለማየሁ፤ በዞኑ ከ310 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመኸር አዝመራ በዘር መሸፈኑን አስታውሰዋል፡፡

በተለያዩ ሰብሎች ከለማው ከዚሁ መሬት ከ6 ሚሊዮን 800 ሺህ ኩንታል በላይ አጠቃላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱንም ነው የተናገሩት።

እስካሁን ከዞኑ ሁሉም ወረዳዎች ከ5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የበቆሎ፣ ስንዴ፣ ጤፍና ቦለቄን ጨምሮ የሌሎች ሰብሎች ምርት መሰብሰቡን አመልክተዋል፡፡

ከተሰበሰበው ምርት ውስጥ ከ985 ሺህ ኩንታል በላይ የሚሆነው የስንዴ ምርት መሆኑን ገልጸው ዘንድሮ ከዞኑ ለመሰብሰብ የታቀደው የሰብል ምርት ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር በ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል፡፡

በጽህፈት ቤቱ የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ታሪኩ ብዛየሁ በበኩላቸው ሙሉ የግብርና ፓኬጅ የተገበሩ አርሶ አደሮች ምርት መጨመሩን አረጋግጠናል ብለዋል፡፡

ፓኬጆቹ የተፈጥሮ ማዳበሪያ መጠቀም፣ ምርጥ ዘር፣ የኩታ ገጠምና የትራክተር አስተራረስ ዘዴ መተግበር ዋና ዋናዎቹ እንደሆኑ አመልክተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026