የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>የናይል ትብብር ማዕቀፍ ስምምነት ሁሉን አሳታፊ የውሃ ሀብት ልማት ትብብር የሚፈጥር ነው - ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር)</p>

Jan 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡- ወደ ትግበራ ምዕራፍ የገባው የናይል ትብብር ማዕቀፍ ስምምነት ሁሉንም የተፋሰሱን ሀገራት ያካተተ የውሃ ሀብት ልማት ትብብር የሚፈጥር መሆኑን የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ።

ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ እና አፍሪካ ህብረት የጀርመን አምባሳደር ሀንስ ሀንፊልድን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

በውይይቱ ወቅት ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ንጹህ አረንጓዴ ኢነርጂ በማምረት ቀጣናውን በኃይል ለማስተሳሰር እያከናወነች ያለው ስራ ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል።

በስድስት ሀገራት ፀድቆ ወደ ስራ የገባው የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ሁሉም የተፋሰሱ ሀገራትን አሳታፊ ያደረገ የውሃ ልማት ትብብር ለመፍጠር እንደሚያስችልም አመልክተዋል።

በሌላ በኩል በውሃ ሀብት ልማት በተከናወኑ ስራዎች ከ74 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ነው ሚኒስትሩ የጠቆሙት።

የጀርመን መንግስት በኢነርጂ ልማት ዘርፍ፤ በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና በውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ድጋፍ እንደሚያርግ ጠቅሰው፤ በተለይ ጂአይዜድ በገጠር የሀገሪቱ ክፍል ኤሌኬትሪክ ለማዳረስ ለረጅም ጊዜ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን አንስተዋል።

በቀጣይም ከዋና የሀይል መስመር ርቀው የሚገኙ ገጠራማ አካባቢዎችን የኦፍግሪድ ኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ ድጋፍ እንዲያደርጉም ጠይቀዋል፡፡

በኢትዮጵያ እና አፍሪካ ህብረት የጀርመን አምባሳደር ሀንስ ሀንፊልድ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ልማት ላይ አበረታች ስራ እያከናወነች መሆኑን ገልጸው የቀጣናዊ የኃይል ትስስሩ ዘርፈ ብዙ ትብብርን እንደሚፈጥርም አመልክተዋል።

በሌላ በኩል አምባሳደሩ በኢትዮጵያ ጠንካራ የኢኮኖሚ ሪፎርም እየተደረገ መሆኑን መግለጻቸውን ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026