
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡- ወደ ትግበራ ምዕራፍ የገባው የናይል ትብብር ማዕቀፍ ስምምነት ሁሉንም የተፋሰሱን ሀገራት ያካተተ የውሃ ሀብት ልማት ትብብር የሚፈጥር መሆኑን የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ እና አፍሪካ ህብረት የጀርመን አምባሳደር ሀንስ ሀንፊልድን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በውይይቱ ወቅት ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ንጹህ አረንጓዴ ኢነርጂ በማምረት ቀጣናውን በኃይል ለማስተሳሰር እያከናወነች ያለው ስራ ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል።
በስድስት ሀገራት ፀድቆ ወደ ስራ የገባው የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ሁሉም የተፋሰሱ ሀገራትን አሳታፊ ያደረገ የውሃ ልማት ትብብር ለመፍጠር እንደሚያስችልም አመልክተዋል።
በሌላ በኩል በውሃ ሀብት ልማት በተከናወኑ ስራዎች ከ74 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ነው ሚኒስትሩ የጠቆሙት።
የጀርመን መንግስት በኢነርጂ ልማት ዘርፍ፤ በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና በውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ድጋፍ እንደሚያርግ ጠቅሰው፤ በተለይ ጂአይዜድ በገጠር የሀገሪቱ ክፍል ኤሌኬትሪክ ለማዳረስ ለረጅም ጊዜ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን አንስተዋል።
በቀጣይም ከዋና የሀይል መስመር ርቀው የሚገኙ ገጠራማ አካባቢዎችን የኦፍግሪድ ኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ ድጋፍ እንዲያደርጉም ጠይቀዋል፡፡
በኢትዮጵያ እና አፍሪካ ህብረት የጀርመን አምባሳደር ሀንስ ሀንፊልድ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ልማት ላይ አበረታች ስራ እያከናወነች መሆኑን ገልጸው የቀጣናዊ የኃይል ትስስሩ ዘርፈ ብዙ ትብብርን እንደሚፈጥርም አመልክተዋል።
በሌላ በኩል አምባሳደሩ በኢትዮጵያ ጠንካራ የኢኮኖሚ ሪፎርም እየተደረገ መሆኑን መግለጻቸውን ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026