የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በዞኖቹ በተያዘው የበጋ ወቅት ከ137 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ስንዴ ይለማል</p>

Jan 21, 2025

IDOPRESS

ነገሌ ቦረና/ቡሌ ሆራ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ እና ምሥራቅ ቦረና ዞኖች በዘንድሮው የበጋ ወቅት 137 ሺህ በላይ መሬት በመስኖ ስንዴ በማልማት ከ3 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን የዞኖቹ ግብርና ጽህፈት ቤቶች ገለፁ።


የምዕራብ ጉጂ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ሃላፊ ከራ ዳዲ(ዶ/ር) እንዳሉት በዞናቸው በዘንድሮው የበጋ ወቅት 103 ሺህ 738 ሄክታር መሬት በመስኖ ስንዴ ለማልማት ታቅዶ እስካሁን በዘጠኝ ወረዳዎች ከ94 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን ገልጸዋል።፡

ምርታማነቱን ለማሳደግም ከ94 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘርና ከ100 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ጥቅም ላይ መዋሉን ገልጸው፤ 73 ሺህ 192 አልሚ አርሶ አደሮች ሙያዊ እገዛ ተደርጎላቸዋል ብለዋል።

በዞኑ በበጋ ስንዴ ልማት ከ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱንም እንዲሁ፡፡


የምስራቅ ቦረና ዞን ግብርና ፅህፈት ቤት የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ቦነያ ጎሎ በበኩላቸው እንዳሉት ምሥራቅ ቦረና ከክልሉ ዝናብ አጠር አካባቢዎች አንዱ መሆኑን ገልፀው፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከእንስሳት እርባታ ጎን ለጎን በስንዴ ሰብል ልማት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመረው ጥረት ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል።

በተያዘው የበጋ ወቅት 33 ሺህ 440 ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ በስንዴ ለማልማት ታቅዶ እስካሁን ከ20 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በስንዴ በዘር ተሸፍኗል ብለዋል።

በልማቱ በመሳተፍ ላይ ላሉ 20 ሺህ 816 አርሶ አደሮች የቀረበ 1 ሺህ 248 ኩንታል ምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ ጥቅም ላይ መዋሉን ገልጸው፤ ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ተናግረዋል።


ኢዜአ ካነጋገራቸው አርሶ አደሮች መካከል በምዕራብ ጉጂ ዞን የቀርጫ ወረዳ ነዋሪ አቶ ገመቹ ባቲ እና አዶላ በራቆ የመስኖ የሰብል ልማቱ እምብዛም የተለመደ ባለመሆኑ ዝናብ ጠብቀው በሚያለሙት ሰብል ከእጅ ወደ አፍ ሆኖ መቆየቱን ገልጸዋል።


ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የበጋ መስኖ ስንዴ ማልማት እየተለመደና ባህል እየሆነ መጣቱን ገልጸው፤ ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በመተባበር በኩታ ገጠም የበጋ መስኖ ስንዴ እያለሙ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026