የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በዞኖቹ በተያዘው የበጋ ወቅት ከ137 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ስንዴ ይለማል</p>

Jan 21, 2025

IDOPRESS

ነገሌ ቦረና/ቡሌ ሆራ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ እና ምሥራቅ ቦረና ዞኖች በዘንድሮው የበጋ ወቅት 137 ሺህ በላይ መሬት በመስኖ ስንዴ በማልማት ከ3 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን የዞኖቹ ግብርና ጽህፈት ቤቶች ገለፁ።


የምዕራብ ጉጂ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ሃላፊ ከራ ዳዲ(ዶ/ር) እንዳሉት በዞናቸው በዘንድሮው የበጋ ወቅት 103 ሺህ 738 ሄክታር መሬት በመስኖ ስንዴ ለማልማት ታቅዶ እስካሁን በዘጠኝ ወረዳዎች ከ94 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን ገልጸዋል።፡

ምርታማነቱን ለማሳደግም ከ94 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘርና ከ100 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ጥቅም ላይ መዋሉን ገልጸው፤ 73 ሺህ 192 አልሚ አርሶ አደሮች ሙያዊ እገዛ ተደርጎላቸዋል ብለዋል።

በዞኑ በበጋ ስንዴ ልማት ከ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱንም እንዲሁ፡፡


የምስራቅ ቦረና ዞን ግብርና ፅህፈት ቤት የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ቦነያ ጎሎ በበኩላቸው እንዳሉት ምሥራቅ ቦረና ከክልሉ ዝናብ አጠር አካባቢዎች አንዱ መሆኑን ገልፀው፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከእንስሳት እርባታ ጎን ለጎን በስንዴ ሰብል ልማት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመረው ጥረት ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል።

በተያዘው የበጋ ወቅት 33 ሺህ 440 ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ በስንዴ ለማልማት ታቅዶ እስካሁን ከ20 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በስንዴ በዘር ተሸፍኗል ብለዋል።

በልማቱ በመሳተፍ ላይ ላሉ 20 ሺህ 816 አርሶ አደሮች የቀረበ 1 ሺህ 248 ኩንታል ምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ ጥቅም ላይ መዋሉን ገልጸው፤ ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ተናግረዋል።


ኢዜአ ካነጋገራቸው አርሶ አደሮች መካከል በምዕራብ ጉጂ ዞን የቀርጫ ወረዳ ነዋሪ አቶ ገመቹ ባቲ እና አዶላ በራቆ የመስኖ የሰብል ልማቱ እምብዛም የተለመደ ባለመሆኑ ዝናብ ጠብቀው በሚያለሙት ሰብል ከእጅ ወደ አፍ ሆኖ መቆየቱን ገልጸዋል።


ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የበጋ መስኖ ስንዴ ማልማት እየተለመደና ባህል እየሆነ መጣቱን ገልጸው፤ ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በመተባበር በኩታ ገጠም የበጋ መስኖ ስንዴ እያለሙ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዞኑ የመኸር አዝመራን ውጤታማ  ለማድረግ ለኩታ ገጠም እርሻና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩረት ተሰጥቷል

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...

Jul 23, 2026

የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያልቁ ተግባራት ይጠናከራሉ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...

Jul 22, 2026

በድሬደዋ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወሰዱ

ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...

Jul 21, 2026

መንግሥት የሎጂስቲክስ ዘርፉን በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...

Jul 15, 2026