የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>ድርጅቱ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግን መቀላቀሉ ትርፋማነቱን ለማጎልበት ዕድል ይፈጥርለታል- አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ</p>

Jan 22, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮ-ኢንጂነሪግ ግሩፕ ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግን መቀላቀሉ ድርጅቱ ይበልጥ ትርፋማ እንዲሆን መልካም ዕድል እንደሚያመጣለት የግሩፑ ዋና ስራ አስፈጻሚ አምባሳደር ሱሌይማን ገለፁ።

የኢትዮ-ኢንጂነሪግ ግሩፕ በቅርቡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ከተቀላቀሉ ስምንት የመንግስት ልማት ድርጅቶች አንዱ ነው።

በ2002 ዓ.ም ብረታ ብረት ኢንጂነሪግ ኮርፖሬሽን(ሜቴክ) በሚል ይታወቅ የነበረው ይህ ተቋም በ2013 ዓ.ም በተሰራው ሪፎርም ኢትዮ-ኢንጂነሪግ ግሩፕ በሚል ስያሜ ዳግም መደራጀቱ ይታወሳል።

የኢትዮ-ኢንጂነሪግ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ኩባንያው ከተቆጣጣሪነት ወጥቶ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግን መቀላቀሉ መልካም ዕድል ነው ብለዋል።

ይህም በቀጣይነት ያሉበትን ተግዳሮቶች እየቀረፈ ይበልጥ ትርፋማ ድርጅት ለመሆን ያግዘዋል የሚል እምነት አላቸው።

የኢትዮ-ኢንጂነሪግ ግሩፕ ተኪ ምርቶችን በማምረት የውጭ ምንዛሬ ወጪን ከሚያድኑ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፎች ወሳኝ ድርሻ ይዟል።

ግሩፑ እስካሁን 35 ፋብሪካዎችን ያላቸው ዘጠኝ አምራች ኢንዱስትሪዎች የመደገፍ፣ የመከታተልና የግብዓት ችግሮችን በመሙላት የተቆጣጣሪነት ሚና እንደነበረው ገልጸዋል።

ፋብሪካዎቹ እንደ ብረት፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ታወሮች፣ የእርሻ ተሽከርካሪዎችና ፕላስቲክና መሰል ተኪ ምርቶችን የሚያመርቱ እንደሆኑ አንስተዋል።

ከተኪ ምርቶች ባሻገርም በቴክኖሎጂና ዕውቀት ሽግግር ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ስለመሆኑ አንስተዋል።

በዚህም ግሩፑ በ2013 ዓ. ም አሁን የያዘውን ስያሜ ይዞ ዳግም ከተቋቋመ በኋላ ከኪሳራ ወደ ትርፋማነት እየተሸጋገረ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ለአብነትም በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ ማሳካቱን ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026