የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>የሎጂስቲክስ ዘርፉ የአገር ኢኮኖሚን እንዲደግፍ ለማድረግ በትኩረት ይሰራል - አለሙ ስሜ(ዶ/ር)</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ጥር 28/2017(ኢዜአ)፦ የሎጂስቲክስ ዘርፉ የአገር ኢኮኖሚን መደገፍ እንዲችል የአፈጻጸምና የአደረጃጀት ችግሮችን ለመፍታት እየተሰራ መሆኑን የትራንስፖርት ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ(ዶ/ር) ገለጹ።

ሚኒስቴሩ ለሁሉም ክልሎችና ለሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የሎጂስቲክስ አመራር አባላትና ባለሙያዎች በአዳማ ከተማ ለሁለት ቀናት ያዘጋጀው የስልጠና መድረክ ማምሻውን ተጠናቋል።


ሚኒስትሩ በማጠቃለያው ላይ እንደገለጹት የሎጂስቲክስ ዘርፉ በመሰረተ ልማት እጥረት፣ ህገ ወጥ የኬላዎች መበራከት፣ በጭነት ተሽከርካሪዎች ቁጥር ማነስና በሌሎች ችግሮች ምክንያት የሚፈለገውን ያህል ውጤታማ አልሆነም።

የሎጂስቲክስ ዘርፉ የአገር ኢኮኖሚን መደገፍ እንዲችል የአፈጻጸምና የአደረጃጀት ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

በክልሎች የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ መሆኑን አመልክተው ይህ ስልጠናም የዚሁ እንቅስቃሴ አካል እንደሆነ አስረድተዋል።

በመንግሥት በኩል የሚደረጉ ማሻሻያዎችን ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገቢው መንገድ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።

በሚኒስቴሩ ሎጂስቲክስና መሠረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ዴንጌ ቦሩ በበኩላቸው እንደ ሀገር የሎጂስቲክስ አፈጻጸም እንዲሻሻል በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።


ዘርፉን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች እንደሚጠናከሩ የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላትም ያልተቆጠበ ተሳትፎና ጥረት ማድረግ አለባቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.