
ሮቤ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፡- ባለፉት ዓመታት ያከናወኗቸው የተፋሰስ ልማት ስራዎች ምርታማነታቸውን እያሳደገላቸው መሆኑን በኦሮሚያ ክልል የባሌ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ፡፡
የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት በበኩሉ በዞኑ 105 ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍኑ 320 ተፋሰሶች ተለይተው በዘንድሮው የበጋ ወራት እየለሙ መሆኑን ገልጿል።
ኢዜአ ካነጋገራቸው የዞኑ አርሶ አደሮች መካከል አርሶ አደር ሁሴን በከር በሰጡት አስተያየት በቀደሙት ዓመታት መሬታቸው በጎርፍ በመሸርሸሩ ምርታቸው መቀነሱን አስታውሰዋል።
ችግሩን ለመፍታትም የአካባቢው ማህበረሰብ በነቂስ ወጥቶ በቅንጅት ያከናወናቸው የተቀናጀ የተፈጥሮ ኃብት ልማት ስራዎች የተራቆተ መሬታቸው ለምነቱ እንዲመለስ አግዟል።
በዚህም ከግማሽ ሄክታር መሬታቸው ላይ የሚያገኙት ምርት እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።
አርሶ አደር አብዱረህማን ማህሙድ በበኩላቸው ባለፉት ዓመታት በአካባቢያቸው በተከናወኑ የተፋሰስ ልማት ስራዎች በበጋ ወቅት ደርቀው የነበሩ ምንጮች ጎልብተው ዓመቱን ሙሉ እንዲፈሱ ማድረጉን ተናግረዋል።
ይህ ደግሞ ለግብርናም ሆነ ለእንስሳት ልማት ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ ምርትና ምርታማነታቸው እንዲጨምር አወንታዊ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ነው ያነሱት።
የተፋሰስ ልማት ስራዎቹ ባስገኙት ፋይዳም የአካባቢያቸው ማህበረሰብ በየዓመቱ በነቂስ ወጥቶ የመስራት ፍላጎቱ እንዲጨምር ማድረጉን ተናግረዋል።
የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራው በተለይም የጎርፍና የአፈር መከላትን በማስቀረቱ ተመናምኖ የነበረው የተፈጥሮ ደን እያገገመ በመምጣቱ ለግብርና ሥራችን እያገዘን ነው ያሉት ደግሞ አርሶ አደር ቃሲም ሲራጅ ናቸው።
የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሰለሞን ዳዲ በበኩላቸው በዞኑ በዘንድሮ የበጋ ወራት የተፋሰስ ልማት ስራዎች ከ320 የሚበልጡ ተፋሰሶችን መሰረት ያደረጉ ስራዎች እየለሙ ናቸው፡፡
በዚህም በተለያዩ ምክንያቶች የተጎዳ 20 ሺህ ሄክታር መሬት ከንክኪ ነፃ ከማድረግ ባለፈ 87ሺህ እርከኖችና ሌሎች የተለያዩ የተቀናጁ ስራዎች አንደሚከናወኑ ገልጸዋል፡፡
በዞኑ ለሁለት ወራት በዘመቻ በሚካሄደው የተቀናጀ የተፈጥሮ ኃብት ልማት ሥራ 105 ሺህ ሄክታር መሬትን የሚያካልል ሥራ እንደሚከናወን ከጽህፈት ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...
Jul 22, 2026
ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...
Jul 21, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...
Jul 15, 2026