የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>ሀገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን አስተዋፅዖ ወሳኝ ነው - ቋሚ ኮሚቴው</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፡- ሀገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን አስተዋፅዖ ወሳኝ መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት፣ ስራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ።

ቋሚ ኮሚቴው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርን የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወር የዕቅድ አፈፃፀም ገምግሟል።

በሪፖርቱ የቀረበው ዕቅድ አፈፃፀም የተሻለ ጥንካሬዎች የታዩበት መሆኑን ቋሚ ኮሚቴው ጠቁሟል።

በተጨማሪም በእጥረትና ትኩረት ይሻሉ ያላቸው ጉዳዮችን በቀጣይ በመስራት አፈፃፀማቸውን ማሻሻል እንደሚገባም አመላክቷል።


የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ነገሬ ሌንጮ(ዶ/ር) ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መንግስት የያዘውን እቅድ ከግብ ለማድረስ ትልቅ ሚና ይጫወታል ብለዋል።

ከድህነት ለመውጣትና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑ ጠቁመው ተቋሙ ታዳጊ ወጣቶችን ለማበረታታት የሚሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ከአመራር አንፃር የተነሱ አንዳንድ ቅሬታዎችን በሚመለከት ስብጥሩን የጠበቀ፣ ከጥገኝነት ነፃ እና እውነትን መሰረት በማድረግ የሚሰራ የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ በማቋቋም መፍታት እንደሚገባ አሳስበዋል።

ቋሚ ኮሚቴው በሪፖርቱ ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችን ያነሳ ሲሆን የሚንስቴሩ የስራ ሀላፊዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል።


የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ለማሻሻል ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ከኢኖቬሽን አንፃር የተለያዩ የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎችን አካታች በማደረግ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑም አብራርተዋል።

የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተቋማትን ከማገዝ እና እሴቶችን ከማበልፀግ አንፃር ግብርናን እና ጤናን ጨምሮ የተለያዩ ዘርፎችን በማካተት በርካታ ሰራዎች እየተሰሩ መሆኑን ማስረዳታቸውን ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዞኑ የመኸር አዝመራን ውጤታማ  ለማድረግ ለኩታ ገጠም እርሻና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩረት ተሰጥቷል

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...

Jul 23, 2026

የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያልቁ ተግባራት ይጠናከራሉ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...

Jul 22, 2026

በድሬደዋ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወሰዱ

ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...

Jul 21, 2026

መንግሥት የሎጂስቲክስ ዘርፉን በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...

Jul 15, 2026