
አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፡- ሀገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን አስተዋፅዖ ወሳኝ መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት፣ ስራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ።
ቋሚ ኮሚቴው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርን የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወር የዕቅድ አፈፃፀም ገምግሟል።
በሪፖርቱ የቀረበው ዕቅድ አፈፃፀም የተሻለ ጥንካሬዎች የታዩበት መሆኑን ቋሚ ኮሚቴው ጠቁሟል።
በተጨማሪም በእጥረትና ትኩረት ይሻሉ ያላቸው ጉዳዮችን በቀጣይ በመስራት አፈፃፀማቸውን ማሻሻል እንደሚገባም አመላክቷል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ነገሬ ሌንጮ(ዶ/ር) ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መንግስት የያዘውን እቅድ ከግብ ለማድረስ ትልቅ ሚና ይጫወታል ብለዋል።
ከድህነት ለመውጣትና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑ ጠቁመው ተቋሙ ታዳጊ ወጣቶችን ለማበረታታት የሚሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
ከአመራር አንፃር የተነሱ አንዳንድ ቅሬታዎችን በሚመለከት ስብጥሩን የጠበቀ፣ ከጥገኝነት ነፃ እና እውነትን መሰረት በማድረግ የሚሰራ የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ በማቋቋም መፍታት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ቋሚ ኮሚቴው በሪፖርቱ ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችን ያነሳ ሲሆን የሚንስቴሩ የስራ ሀላፊዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ለማሻሻል ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ከኢኖቬሽን አንፃር የተለያዩ የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎችን አካታች በማደረግ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑም አብራርተዋል።
የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተቋማትን ከማገዝ እና እሴቶችን ከማበልፀግ አንፃር ግብርናን እና ጤናን ጨምሮ የተለያዩ ዘርፎችን በማካተት በርካታ ሰራዎች እየተሰሩ መሆኑን ማስረዳታቸውን ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...
Jul 22, 2026
ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...
Jul 21, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...
Jul 15, 2026