የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>ሀገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን አስተዋፅዖ ወሳኝ ነው - ቋሚ ኮሚቴው</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፡- ሀገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን አስተዋፅዖ ወሳኝ መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት፣ ስራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ።

ቋሚ ኮሚቴው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርን የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወር የዕቅድ አፈፃፀም ገምግሟል።

በሪፖርቱ የቀረበው ዕቅድ አፈፃፀም የተሻለ ጥንካሬዎች የታዩበት መሆኑን ቋሚ ኮሚቴው ጠቁሟል።

በተጨማሪም በእጥረትና ትኩረት ይሻሉ ያላቸው ጉዳዮችን በቀጣይ በመስራት አፈፃፀማቸውን ማሻሻል እንደሚገባም አመላክቷል።


የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ነገሬ ሌንጮ(ዶ/ር) ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መንግስት የያዘውን እቅድ ከግብ ለማድረስ ትልቅ ሚና ይጫወታል ብለዋል።

ከድህነት ለመውጣትና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑ ጠቁመው ተቋሙ ታዳጊ ወጣቶችን ለማበረታታት የሚሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ከአመራር አንፃር የተነሱ አንዳንድ ቅሬታዎችን በሚመለከት ስብጥሩን የጠበቀ፣ ከጥገኝነት ነፃ እና እውነትን መሰረት በማድረግ የሚሰራ የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ በማቋቋም መፍታት እንደሚገባ አሳስበዋል።

ቋሚ ኮሚቴው በሪፖርቱ ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችን ያነሳ ሲሆን የሚንስቴሩ የስራ ሀላፊዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል።


የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ለማሻሻል ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ከኢኖቬሽን አንፃር የተለያዩ የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎችን አካታች በማደረግ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑም አብራርተዋል።

የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተቋማትን ከማገዝ እና እሴቶችን ከማበልፀግ አንፃር ግብርናን እና ጤናን ጨምሮ የተለያዩ ዘርፎችን በማካተት በርካታ ሰራዎች እየተሰሩ መሆኑን ማስረዳታቸውን ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026