
ጂንካ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፡- ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማር ሥራው ጎን ለጎን በጥናትና ምርምር የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመራቸውን ሥራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥል የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ እና የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ።
አቶ አገኘሁ ተሻገር እና የሥራ አመራር ቦርድ አባላት የዩኒቨርሲቲውን የስድስት ወራት አፈፃፀም ገምግመዋል።

አቶ አገኘሁ በዚህን ጊዜ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ከተቋቋመ ጥቂት ዓመታት ቢሆነውም ከመማር ማስተማር ስራው ጎን ለጎን የአካባቢው ማህበረሰብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ሥራዎችን ሰርቷል።
ዩኒቨርሲቲው በጥናትና ምርምር ሥራዎቹ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።
በተለይ በአካባቢው ያለውን የእንስሳት ሀብት ዝርያ በማሻሻል የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
የዩኒቨርሲቲው ምሁራን ችግር ፈቺ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በማጠናከር ማህበረሰቡን እንዲያግዙም አስገንዝበዋል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ኩሴ ጉድሼ(ዶ/ር) በበኩላቸው ከሥራ አመራር ቦርድ አባላት ጋር በተካሄደው ግምገማ የተነሱ የአፈጻጸም ክፍተቶችን በመሙላት ጥናካሬዎችን በማስቀጠል ዩኒቨርሲቲው የተጣለበትን ሀገራዊ ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት ተግተን እንሰራለን ብለዋል።
በግምገማ መድረኩ ላይ የአካባቢው አመራር አባላትና የማህበረሰብ ተወካዮች ታድመዋል።
ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...
Jul 22, 2026
ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...
Jul 21, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...
Jul 15, 2026