
ጂንካ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፡- ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማር ሥራው ጎን ለጎን በጥናትና ምርምር የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመራቸውን ሥራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥል የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ እና የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ።
አቶ አገኘሁ ተሻገር እና የሥራ አመራር ቦርድ አባላት የዩኒቨርሲቲውን የስድስት ወራት አፈፃፀም ገምግመዋል።

አቶ አገኘሁ በዚህን ጊዜ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ከተቋቋመ ጥቂት ዓመታት ቢሆነውም ከመማር ማስተማር ስራው ጎን ለጎን የአካባቢው ማህበረሰብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ሥራዎችን ሰርቷል።
ዩኒቨርሲቲው በጥናትና ምርምር ሥራዎቹ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።
በተለይ በአካባቢው ያለውን የእንስሳት ሀብት ዝርያ በማሻሻል የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
የዩኒቨርሲቲው ምሁራን ችግር ፈቺ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በማጠናከር ማህበረሰቡን እንዲያግዙም አስገንዝበዋል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ኩሴ ጉድሼ(ዶ/ር) በበኩላቸው ከሥራ አመራር ቦርድ አባላት ጋር በተካሄደው ግምገማ የተነሱ የአፈጻጸም ክፍተቶችን በመሙላት ጥናካሬዎችን በማስቀጠል ዩኒቨርሲቲው የተጣለበትን ሀገራዊ ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት ተግተን እንሰራለን ብለዋል።
በግምገማ መድረኩ ላይ የአካባቢው አመራር አባላትና የማህበረሰብ ተወካዮች ታድመዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026