የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በ26ኛው የዓለም እንስሳት ጤና የአፍሪካ አህጉራዊ ጉባኤ ላይ የተሳተፉ የዘርፉ ባለሙያዎች የእንስሳት ጤና ተቋማትንና የልማት ስራዎችን ጎበኙ</p>

Feb 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦ በ26ኛው የዓለም እንስሳት ጤና የአፍሪካ አህጉራዊ ጉባኤ ላይ የተሳተፉ የዘርፉ ባለሙያዎች የእንስሳት ጤና ተቋማትንና የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።

26ኛው የዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት የአፍሪካ አህጉራዊ ጉባኤ የእንስሳት ጤናን ማሻሻል በሚያስችሉ አጀንዳዎች ላይ ላለፉት ሶስት ቀናት በአዲስ አበባ ተከናውኖ ተጠናቋል፡፡

የጉባኤውን መጠናቀቅ ተከትሎም ተሳታፊዎቹ በኢትዮጵያ ያሉ የእንስሳት ጤናና የተለያዩ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡


ጉብኝቱ በቢሾፍቱ ብሄራዊ የእንስሳት ጤና ኢንስቲትዩት፣ የአፍሪካ ህብረት የፓን አፍሪካ የእንስሳት ህክምና ክትባት ማዕከል/AU-PANVAC/ እና ኤልፎራ አግሮ ኢንዱስትሪን ያካተተ ሲሆን በአዲስ አበባ ደግሞ የአንድነት ፓርክን ተመልክተዋል፡፡

ተሳታፊዎቹ ብሄራዊ የእንስሳት ጤና ኢንስቲትዩትን በጎበኙበት ወቅት ኢንስቲትዩቱ ለእንስሳት በሽታዎች ክትባት ማምረትን፣ ልዩ ልዩ የእንስሳት መድኃኒቶች ማቀነባበርን፣ የክትባትና መድኃኒት ምርቶችን ለውጭ ገበያ ማቅረብና ሌሎች በሚሰራቸው ተያያዥ ስራዎች ላይ ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡


በተጨማሪም መቀመጫውን በኢትዮጵያ ያደረገው የፓን አፍሪካ የእንስሳት ህክምና ክትባት ማዕከል/AU-PANVAC/ የደስታ በሽታን ለመከላከል ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በአፍሪካ የእንስሳት ጤናን ለማሻሻል ጥራት ያለው ክትባትና ምርመራ መጠቀምን በማበረታታት ላይ እንደሚገኝ ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል፡፡

ከዚህ ጎን ለጎን በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ትኩረት ካደረገባቸው የእንስሳት ልማቶች አንዱ እንቁላልና ዶሮ ሲሆን ኤልፎራ አግሮ ኢንዱስትሪ እያከናወነ ያለውን የዶሮ እርባታን ጎብኝተዋል፡፡


በመስክ ምልከታው ሰፊና በርካታ የእንስሳት ጤናና ልማት ተሞክሮዎችን እንዲሁም ልምዶችን እንዳገኙ ተሳታፊዎቹ መናገራቸውን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.