የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>ጨፌ ኦሮሚያ ወቅታዊ መረጃዎችን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል የሞባይል መተግበሪያ ይፋ አደረገ</p>

Feb 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- ጨፌ ኦሮሚያ ለአባላቱና ለህብረተሰቡ ወቅታዊ መረጃዎችን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል የሞባይል መተግበሪያ በይፋ አስጀምሯል።


መተግበሪያው ጨፌው ለአባላቱ ወቅታዊ መረጃዎችን ለመስጠት እንዲሁም በጊዜና በቦታ ያልተገደቡ መረጃዎችን ተደራሽ በማድረግ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲጠናከር ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑም ተጠቁሟል።


በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱራህማን፣ የጨፌው አባላትን ጨምሮ ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።

አፈ-ጉባኤዋ ሰዓዳ አብዱራህማን በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የሞባይል መተግበሪያው የጨፌው አባላት የሕዝብ ውክልና ስራቸውን በቀላሉ እንዲወጡ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።

የጨፌው አባላት የጉባኤ አጀንዳዎችን፣ በጨፌው የተላለፉ ውሳኔዎችን ብሎም የተለያዩ መረጃዎችን በጊዜ እና በቦታ ሳይገደቡ እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል።

በተጨማሪም ከሕብረተሰቡ የሚነሱ ጥያቄዎችን የሚመለከታቸው አካላት ምላሽ እንዲሰጡ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል።


የሞባይል መተግበሪያው የወረቀት አሰራሮችን የሚያስቀር እና ዲጂታል አሰራሮችን ከማስፋፋት አኳያ ትልቅ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል።

መተግበሪያው በዋናነት አምስት ትልልቅ መነሻዎችን(menu) የያዘ ሲሆን ሕጎች፣ ቀን መቁጠሪያ፣ ወቅታዊ ዜናዎችን፣ የጨፌውን አባላት ስም ዝርዝር እና የቋሚ ኮሚቴ አባላትን እንዲሁም ሴቲንግ ያለው መሆኑም ተጠቁሟል።

ጨፌው የሞባይል መተግበሪያውን ከኔዘርላንድስ ኢንስቲትዩት ፎር መልቲፓርቲ ዲሞክራሲ ተቋም ጋር በመተባበር ያበለጸገ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ ስራ ላይ እንደሚውልም ተጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026