የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በኦሮሚያ ክልል የእደ ጥበብ ማዕከላትን ከሥራ ዕድል መፍጠሪያነት ባለፈ የቱሪዝም ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ ነው - የክልሉ ቱሪዝም ኮሚሽን</p>

Feb 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የእደ ጥበብ ማዕከላትን ከሥራ ዕድል መፍጠሪያነት ባለፈ የቱሪዝም ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ቱሪዝም ኮሚሽን ገልጿል።

የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ኮሚሽነር ለሊሴ ዱጋ እና ሌሎች የሥራ ሀላፊዎች በሸገር ከተማ ለገጣፎ ለገዳዲ ክፍለ ከተማ የክህሎት ማጎልበቻ ማዕከልን ጎብኝተዋል።


ኮሚሽነር ላሊሴ ዱጋ ጉብኝቱ ላይ እንደተናገሩት የእደ ጥበብ ሥራ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠር በሻገር ለቱሪዝም ገበያ ትልቅ አቅም ነው።

በተለይም የባህል አልባሳትን ጨምሮ ሌሎች የእደ ጥበብ ውጤቶች ተጨማሪ የቱሪስት መስህብ በመሆናቸው በዘርፉ ለተሰማሩትም ገቢ ይፈጥራሉ ብለዋል።

ኮሚሽኑ በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች የሚታወቁ የእደ ጥበብ ውጤቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ የቱሪዝም አቅም እንዲሆኑ የበኩሉን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

በሸገር ከተማ ለገጣፎ ለገዳዲ ክፍለ ከተማ አስተዳዳሪ አቶ ጫላ አዳሬ በበኩላቸው በክፍለ ከተማው በርካታ የእደ ጥበብ ማምረቻ ማዕከላት እንዳሉ ጠቅሰዋል።

እነዚህ ማዕከላት ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሪያ እንዲሆኑ ስልጠናን ጭምሮ በተለያየ መልኩ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል።


በክፍለ ከተማው የሚገኘው ጉዲና ቱምሳ ፋውንዴሽን የወጣቶች ሙያ ማጎልበቻ ማሰልጠኛ ማዕከል ዳይሬክተር ወይዘሮ ሌንሳ ጉዲና ማዕከሉ ወጣቶችን በማደራጀት በሚፈልጉት የእደ ጥበብ የሙያ መስክ በማሰልጠን ሰርተው እንዲጠቀሙ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ማዕከሉ በሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ከ2 ሺህ በላይ ወጣቶችን በተለያዩ ሙያዎች በማሰልጠን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ አቅዶ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

ማዕከሉ በዋናነት ወጣቶችን በሸማ፣ በሸክላና በሌሎች የእደ ጥበብ ሥራዎች እያሰለጠነ መሆኑንም ተናግረዋል።

በማዕከሉ ስልጠና ያገኙ ወጣቶችም በስልጠናው ባገኙት ክህሎት የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026