
ሐረር ፣የካቲት 4/2017 (ኢዜአ) ፡-በሐረር ከተማ በሚከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች የስራ እድል ከማግኘታቸው ባሻገር የስራ ባህላቸው መቀየሩን በልማቱ የተሰማሩ ዜጎች ተናገሩ።
በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎች ፍጥነትና ጥራትን ጠብቀው እየተከናወኑ ስለመሆኑም ተገልጿል።
በከተማው በአባዲር ፕላዛ የኮሪደር ልማት ስራ በግንበኝነት የተሰማሩት አቶ ደሳለኝ መንግስቴ እንደሚናገሩት፤ በክልሉ የሚከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች የክልሉን ገጽታ እየለወጡ ናቸው።
በከተማው የሚከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከማድረጉ ባለፈ "አዳዲስ የስራ ባህልና ሙያዊ ክህሎትን እንድናገኝ አስችሎናል" ብለዋል።

በጥርብ ድንጋይና በቅርፃቅርጽ ስራ የተሰማራው ወጣት ፈቀደ መንግስቱ እንደሚገልጸው በከተማው በሚከናወነው የኮሪደር ልማት ስራ እሱን ጨምሩ በስሩ ለሚገኙ 14 ወጣቶች የስራ እድል ተፈጥሯል።
የኮሪደር ልማት ስራው ቀደም ሲል "በውስን ሰዓት የምናከናውነውን ስራ በምሽትና በሌሊት በማከናወን የምናገኘው ገቢ እንዲያድግ አድርጓል" ብሏል።

የኮሪደር ልማት ስራው የከተማዋን ልማት ከማፋጠን ባለፈ በስሩ ለሚገኙ 40 ወጣቶች የስራ እድል በመፍጠር "እኔና ወጣቶቹ ከራሳችን አልፈን ቤተሰቦቻችንን እንድንረዳ ያስቻለ ነው" ያሉት ደግሞ በተቋራጭነት የተሰማሩት አቶ ይትባረክ ተመስገን ናቸው።
በተለይም በስራው ላይ የሚመጡ አዳዲስ አሰራሮች "ክህሎት እንድናገኝና የተሻለ ስራ እንድናከናውን አስችሎናል" ሲሉም ተናግረዋል።

በከተማው የአባዲር ፕላዛ የአረንጓዴ ስፍራ የኮሪደር ልማት ግንባታ ስራን የሚያከናውነው የክልሉ የኮንስትራክሽንና መሰረተ ልማት ስራዎች ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ፈቲህ ረመዳን በበኩላቸው በጀጎል ዓለም አቀፍ ቅርስ ዙርያ የሚከናወነው የኮሪደር ልማት ስራ 1 ነጥብ 4 ሄክታር መሬት የሚሸፍን መሆኑን ጠቅሰዋል።
ታህሳስ 15 ቀን 2017 ዓ.ም በተጀመረው ስራም የአረንጓዴ ልማት፣ የመናፈሻ፣ የአንፊ ትያትር፣ የጀጎል ዓለም ዓቀፍ ቅርስን የመጠበቅና ሌሎች የኮሪደር ልማት ሰራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል።
በስራውም 120 ለሚጠጉ ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩን አመልክተዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026