
አዲስ አበባ፤የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፦ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የፋይዳ አገልግሎቶችን አጠቃሎ የያዘ የፋይዳ መተግበሪያ ዛሬ ይፋ አድርጓል።
መተግበሪያው በተቋሙ ባለሙያዎች እንዲለማ መደረጉ የተገለጸ ሲሆን በአንድሮይድ እና በኣይ ኦ ኤስ ኦፕሬቲንግ ሲስተሞች በዛሬው እለት ለዜጎች ይፋ ተደርጓል።
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን አማካሪ አቤኔዘር ፈለቀ፥ ይፋ የተደረገው መተግበሪያ የተለያዩ ሙከራዎች እና የደህንነት ማረጋገጫ የተደረገበት መሆኑን ተናግረዋል።
ይፋ የተደረገው የሞባይል መተግበሪያ ህብረተሰቡ የሚያገኛቸውን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ በተደገፈና ቀልጣፋ በሆነ መንገድ ለመጠቀም የሚያስችል ነው ብለዋል።
መተግበሪያው ዜጎች የጠፋባቸውን ወይም ያልደረሳቸውን የፋይዳ ቁጥር ዳግም ለማግኘት፣የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን በካርድ መልክ አሳትሞ ለመያዝና የካርድ ህትመት ለመጠየቅ ያስችላል።
ከዚህ በተጨማሪ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ለማግኘት በሚመለከተው አካል ሲመዘገቡ የተሳሳተባቸው መረጃ ካለ በስልካቸው ላይ መረጃውን ማስተካከል የሚችሉበትን ሁኔታ የሚፈጥር ነው።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026