
አዲስ አበባ፤የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፦ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የፋይዳ አገልግሎቶችን አጠቃሎ የያዘ የፋይዳ መተግበሪያ ዛሬ ይፋ አድርጓል።
መተግበሪያው በተቋሙ ባለሙያዎች እንዲለማ መደረጉ የተገለጸ ሲሆን በአንድሮይድ እና በኣይ ኦ ኤስ ኦፕሬቲንግ ሲስተሞች በዛሬው እለት ለዜጎች ይፋ ተደርጓል።
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን አማካሪ አቤኔዘር ፈለቀ፥ ይፋ የተደረገው መተግበሪያ የተለያዩ ሙከራዎች እና የደህንነት ማረጋገጫ የተደረገበት መሆኑን ተናግረዋል።
ይፋ የተደረገው የሞባይል መተግበሪያ ህብረተሰቡ የሚያገኛቸውን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ በተደገፈና ቀልጣፋ በሆነ መንገድ ለመጠቀም የሚያስችል ነው ብለዋል።
መተግበሪያው ዜጎች የጠፋባቸውን ወይም ያልደረሳቸውን የፋይዳ ቁጥር ዳግም ለማግኘት፣የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን በካርድ መልክ አሳትሞ ለመያዝና የካርድ ህትመት ለመጠየቅ ያስችላል።
ከዚህ በተጨማሪ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ለማግኘት በሚመለከተው አካል ሲመዘገቡ የተሳሳተባቸው መረጃ ካለ በስልካቸው ላይ መረጃውን ማስተካከል የሚችሉበትን ሁኔታ የሚፈጥር ነው።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026