የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የቡታጅራ ከተማን የኮሪደር ልማት ጎበኙ</p>

Feb 14, 2025

IDOPRESS

የካቲት 6/2017(ኢዜአ)፡-የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቡታጅራ ከተማ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ጎበኙ፡፡

በቡታጅራ ከተማ በሁለት ምዕራፍ የሚጠናቀቅ የ25 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ በመከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል።

በዚህም በመጀመሪያው ምዕራፍ የ17 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የልማት ስራ በፍጥነትና በጥራት በመሰራት ላይ ይገኛል።

በከተማዋ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)፤ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሙስጠፋ ሀሰን፤ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹና ውብ ከማድረግ ባለፈ ለንግድና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ተመራጭ ለማድረግ የሚያስችል ስራ መሆኑን ለጎብኝዎቹ አብራርተዋል።

የከተማዋን የኮሪደር ልማት በእቅዱ መሰረት በጥራትና በፍጥነት አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አንስተዋል።

በጉብኝቱ ላይ ከሚንስትሩ በተጨማሪ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

በኢትዮጵያ የተለያዩ ከተሞችና የገጠር አካባቢዎች ጭምር የኮሪደር ልማት በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ መሆኑ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.