
ደሴ፤ የካቲት 8/2017(ኢዜአ)፡- በደሴ ከተማ ከ105 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ የሚስማር ፋብሪካ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቆ ወደ ምርት ገብቷል።
የደሴ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሽመልስ ጌታቸው፤ ሰላም በማስጠበቅ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጠሉ በመደረጉ በርካታ ፋብሪካዎች ተገንብተው ወደ ምርት እየገቡ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በዕለቱ የተመረቀው ፋብሪካም በክልሉ የግንባታ ዘርፍ ግብዓት በማቅረብ የሚኖረውን አስተዋጽኦ ጠቅሰዋል።
በከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ አለባቸው ሰይድ በበኩላቸው፤ ዘንድሮ ስምንት ፋብሪካዎቹ ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን አስታውሰዋል።
ተኪ ምርት ላይ የተሰማሩት ፋብሪካዎቹ ገበያ የማረጋጋትና የውጭ ምንዛሬ ለማዳን ሚናቸውን ጠቅሰው፤ የተመረቀው ሚስማር ፋብሪካም ለግንባታ ዘርፉ መነቃቃት እንደሚያግዝ ገልጸዋል።
የፋብሪካው ባለቤት አቶ ካሳሁን ፍቅሬ ፋብሪካውን ከ105 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማድረጋቸውን ገልጸው፤ አሁን ላይ በቀን አምስት ቶን ሚስማር እያመረተ መሆኑን ጠቁመዋል።
በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ ሲገባ በቀን እስከ 20 ቶን ሚስማር እንደሚያመርት ጠቅሰው፤ እስካሁን ለ58 ዜጎች የስራ ድል ፈጥሯል ብለዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026