የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በደሴ ከተማ በ105 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባ የሚስማር ፋብሪካ ተመረቀ</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ የካቲት 8/2017(ኢዜአ)፡- በደሴ ከተማ ከ105 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ የሚስማር ፋብሪካ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቆ ወደ ምርት ገብቷል።

የደሴ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሽመልስ ጌታቸው፤ ሰላም በማስጠበቅ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጠሉ በመደረጉ በርካታ ፋብሪካዎች ተገንብተው ወደ ምርት እየገቡ መሆኑን ጠቅሰዋል።


በዕለቱ የተመረቀው ፋብሪካም በክልሉ የግንባታ ዘርፍ ግብዓት በማቅረብ የሚኖረውን አስተዋጽኦ ጠቅሰዋል።

በከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ አለባቸው ሰይድ በበኩላቸው፤ ዘንድሮ ስምንት ፋብሪካዎቹ ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን አስታውሰዋል።

ተኪ ምርት ላይ የተሰማሩት ፋብሪካዎቹ ገበያ የማረጋጋትና የውጭ ምንዛሬ ለማዳን ሚናቸውን ጠቅሰው፤ የተመረቀው ሚስማር ፋብሪካም ለግንባታ ዘርፉ መነቃቃት እንደሚያግዝ ገልጸዋል።

የፋብሪካው ባለቤት አቶ ካሳሁን ፍቅሬ ፋብሪካውን ከ105 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማድረጋቸውን ገልጸው፤ አሁን ላይ በቀን አምስት ቶን ሚስማር እያመረተ መሆኑን ጠቁመዋል።

በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ ሲገባ በቀን እስከ 20 ቶን ሚስማር እንደሚያመርት ጠቅሰው፤ እስካሁን ለ58 ዜጎች የስራ ድል ፈጥሯል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026