
ቡታጅራ፤ የካቲት 8/2017 (ኢዜአ)፦ አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ የሚያገናኙ የሰንበት ገበያዎች እንዲበራከቱ የተደረገው ጥረት ውጤት እያስገኘ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በቡታጅራ ከተማ አስተዳደር አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ የሰንበት የገበያና የንግድ ማዕከላት እንቅስቃሴን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እንዳሉት በተለያዩ አካባቢዎች ከ1 ሺህ 213 በላይ የሰንበት ገበያዎች በማቋቋም ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲቀርብ ተደርጓል።
በዚህም አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ የተቀመጠው አቅጣጫ ተጨባጭ ውጤት እያስገኝ መሆኑን ጠቅሰው ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተረጋጋ ገበያን ለመፍጠር እየተሰራ ያለው ስራ የሚበረታታ መሆኑም አክለዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ዳምጠው በበኩላቸው የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የተቀመጡ ሀገራዊ አቅጣጫዎች በመተግበር ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች የተደራጁ 134 የሰንበት ገበያዎች ከሰንበት እስከ ሰንበት ያለማቋረጥ አገልግሎት እየሰጡና ተጠቃሚ እያደረጉ ይገኛሉ ብለዋል።
አሁን ላይ የሚታየውን የገበያ ዋጋ ውድነትን ለማረጋጋት እያገዘ በመሆኑ መጠናከር አለበት ብለዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የክልልና ከተማ አስተዳደሮች የንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026