የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ የሚያገናኙ የሰንበት ገበያዎች እንዲበራከቱ የተደረገው ጥረት ውጤት እያስገኘ ነው - ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

ቡታጅራ፤ የካቲት 8/2017 (ኢዜአ)፦ አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ የሚያገናኙ የሰንበት ገበያዎች እንዲበራከቱ የተደረገው ጥረት ውጤት እያስገኘ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።

ሚኒስትሩ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በቡታጅራ ከተማ አስተዳደር አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ የሰንበት የገበያና የንግድ ማዕከላት እንቅስቃሴን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እንዳሉት በተለያዩ አካባቢዎች ከ1 ሺህ 213 በላይ የሰንበት ገበያዎች በማቋቋም ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲቀርብ ተደርጓል።

በዚህም አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ የተቀመጠው አቅጣጫ ተጨባጭ ውጤት እያስገኝ መሆኑን ጠቅሰው ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተረጋጋ ገበያን ለመፍጠር እየተሰራ ያለው ስራ የሚበረታታ መሆኑም አክለዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ዳምጠው በበኩላቸው የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የተቀመጡ ሀገራዊ አቅጣጫዎች በመተግበር ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች የተደራጁ 134 የሰንበት ገበያዎች ከሰንበት እስከ ሰንበት ያለማቋረጥ አገልግሎት እየሰጡና ተጠቃሚ እያደረጉ ይገኛሉ ብለዋል።

አሁን ላይ የሚታየውን የገበያ ዋጋ ውድነትን ለማረጋጋት እያገዘ በመሆኑ መጠናከር አለበት ብለዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የክልልና ከተማ አስተዳደሮች የንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.