የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>የሮቤ ከተማን ለነዋሪው ምቹና የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ስራ ውጤታማ እንዲሆን ድጋፋችንን እንቀጥላለን - ነዋሪዎች</p>

Feb 18, 2025

IDOPRESS

ሮቤ፤ የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፡- የሮቤ ከተማን ለነዋሪው ምቹና የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ስኬታማ እንዲሆን ሁለንተናዊ ድጋፍ እንደሚያደርጉ የከተማው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

በሮቤ ከተማ በመጀመሪያው ምዕራፍ የ7 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ከተማ አስተዳደሩ ገልጿል።

የሮቤ ከተማ የኮሪደር ልማትን በማስመልከት ኢዜአ ከነዋሪዎችና የአስተዳደር አካላት ጋር ቆይታ ያደረገ ሲሆን ነዋሪዎቹም ስራውን እንደሚያግዙ አረጋግጠዋል።

ከከተማው ነዋሪዎች መካከል ሐጂ ቃሲም ኡስማን እንዳሉት የኮሪደር ልማቱ ከተማችንን በማዘመን ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ያደርጋታል።

አስተዳደሩ ከተማችንን በማዘመን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እያከናወነ ለሚገኘው የኮሪደር ልማት ስኬታማነት ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት የተጀመረው የኮሪደር ልማት የከተማዋን የቱሪዝምና የንግድ ማዕከልነት የሚያጠናክር ነው ሲሉም ገልጸዋል።

የኮሪደር ልማት የከተሞችን ገፅታ ከመቀየርና ለኑሮ ተስማሚ አካባቢን ከመፍጠር ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥር ፕሮጀክት መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ሌላው የከተማ ነዋሪ ከድር ከማል ናቸው።

የተጀመራው ልማት በአግባቡ ተጠናቆ ከተማዋ ለኑሮ ምቹና ተስማሚ እንድትሆን ከመንግሥት ጎን በመሰለፍ የሚጠበቅብንን ድጋፍ እናደርጋለን ያሉት ደግሞ አቶ ሐይሉ መንግስቱ ናቸው።

የሮቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዲኖ አሚን በበኩላቸው የሚከናወነው የኮርደር ልማት የከተማውን ማስተር ፕላን መሠረት አድርጎ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም የእግረኛና የብስክሌት መንገድ፣ የአረንጓዴ መዝናኛ ቦታዎችንና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን በማቀናጀት የሚተገበር መሆኑን ገልጸዋል።

በከተማው የመጀመሪያው ዙር የኮሪደር ልማት ከ7 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላው ዋና ዋና መንገዶችን ማልማትና ማስዋብ ስራም በቅርቡ ይጀመራል ብለዋል።

በእስከአሁኑ ሂደት ህብረተሰቡ ንብረቱን በፍላጎቱ ከመንገድ ዳር ማንሳቱን ጠቁመው ሌሎች የኢትዮ-ቴሌኮምና የኤሌክትሪክ መስመር ፖሎችን ከመንገድ ዳር የማንሳት ሥራ እየተከናወነ ነው ብለዋል።

የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ለነዋሪ ምቹና ውብ ከማድረግ ባለፈ ለንግድና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ተመራጭ ማድረግ የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል።

የኮሪደር ልማቱን በእቅዱ መሰረት በሚቀጥሉት ሦስት ወራት በጥራት ለማጠናቀቅ የውስጥ ገቢን አሟጦ መሰብሰብና መንግሥት ለሥራው የመደበውን የካፒታል በጀት በማቀናጀት በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026