የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በአማራ ክልል በተያዘው የበጋ ወራት ከ307 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ማልማት ተችሏል-ግብርና ቢሮ</p>

Feb 18, 2025

IDOPRESS

ባህርዳር ፤ደሴ የካቲት 10/2017 – በአማራ ክልል በተያዘው የበጋ ወራት ከ307 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት እስካሁን በመስኖ ማልማት መቻሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።

ቢሮው ከዞን ግብርና መምሪያ ሀላፊዎችና ቡድን መሪዎች ጋር የ2017 ዓ.ም የግማሽ ዓመት እቅድ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ በባህር ዳርና ደሴ ከተሞች ዛሬ አካሂዷል።


በደሴ በተካሄደ መድረክ ላይ የተገኙት የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ቃልኪዳን ሽፈራው እንደገለጹት በተያዘው የበጋ ወራት እስካሁን ከ307 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ማልማት ተችሏል።

ይህም በመኸር ልማት ከሚገኘው ምርት በተጨማሪ በመስኖ ልማት አርሶ አደሩን በማሳተፍ በምግብ ራሱን ከማስቻል ባሻገር ለኢንዱስትሪ ግብአትና ለገበያ የሚተርፍ ምርት እንዲገኝ የሚያስችል ነው ብለዋል።

በተያዘው የበጋ ወራት ከ340 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

እስካሁን ከለማው ከ307 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ውስጥም 191 ሺህ ሄክታር የሚሆነው በበጋ ስንዴ የተሸፈነ ነው ብለዋል።

በባህርዳርና ኮምበልቻ ከተሞች በተካሄዱት መድረኮች የዘርፉ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026