
ባህርዳር ፤ደሴ የካቲት 10/2017 – በአማራ ክልል በተያዘው የበጋ ወራት ከ307 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት እስካሁን በመስኖ ማልማት መቻሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።
ቢሮው ከዞን ግብርና መምሪያ ሀላፊዎችና ቡድን መሪዎች ጋር የ2017 ዓ.ም የግማሽ ዓመት እቅድ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ በባህር ዳርና ደሴ ከተሞች ዛሬ አካሂዷል።

በደሴ በተካሄደ መድረክ ላይ የተገኙት የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ቃልኪዳን ሽፈራው እንደገለጹት በተያዘው የበጋ ወራት እስካሁን ከ307 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ማልማት ተችሏል።
ይህም በመኸር ልማት ከሚገኘው ምርት በተጨማሪ በመስኖ ልማት አርሶ አደሩን በማሳተፍ በምግብ ራሱን ከማስቻል ባሻገር ለኢንዱስትሪ ግብአትና ለገበያ የሚተርፍ ምርት እንዲገኝ የሚያስችል ነው ብለዋል።
በተያዘው የበጋ ወራት ከ340 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
እስካሁን ከለማው ከ307 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ውስጥም 191 ሺህ ሄክታር የሚሆነው በበጋ ስንዴ የተሸፈነ ነው ብለዋል።
በባህርዳርና ኮምበልቻ ከተሞች በተካሄዱት መድረኮች የዘርፉ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026