የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>የባህርዳር ኮሪደር ልማት ተፈጥሯዊ ውበቷን ይበልጥ በመግለጥ ዘመናዊና ተወዳዳሪ ከተማ ያደርጋታል - አሕመዲን መሐመድ(ዶ/ር)</p>

Feb 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦ የባህርዳር ኮሪደር ልማት ተፈጥሯዊ ውበቷን ይበልጥ በመግለጥ ዘመናዊና ተወዳዳሪ ከተማ ያደርጋታል ሲሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተማ ልማት አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

ዶክተር አሕመዲን በባህርዳር ከተማ አመራሮች መሪነት ከክልሉ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን የኮሪደርና የጣና ዳር ልማት ስራዎችን የሳይት ምልከታ ማድረጋቸውን ገልጽዋል።

በዚህም እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ዘመኑን የዋጁ፣ ሁሉም የከተማው ነዋሪ ህብረተሰብ በእኩልነት የሚጠቀምባቸው ናቸው ማለታቸውን ከአማራ ኮሙኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል።


በተለያዩ ነገሮች ተጋርዶ የነበረውን የጣና ሀይቅና ዳርቻ በመክፈት ለነዋሪዎችና ጎብኝዎች እይታ በመግለጥ ሀይቁን ከመንገዱና ከከተማው ጋር የማስተሳሰር ስራ መከናወኑንም ጠቁመዋል።

በኮሪደር ልማቱ የውበትና አረንጓዴ ቦታዎች ልማት፣ የመዝናኛና ማረፊያ ቦታዎች፣ ፋውንቴን፣ መፀዳጃ ቦታዎች፣ የግራ ቀኝ የብስክሌት መንገድና ህዝብ እንደልብ የሚንቀሳቀስበት ዘመናዊ የእግረኞች መንገድ በልዩ ሁኔታ ያካተተ መሆኑን መመልከታቸውንም ነው ያስታወቁት፡፡


በቀንና በምሽት እየተከናወነ ያለውን ስራ እያስተባበሩ የሚገኙ የከተማው አመራሮችንና ባለሙያዎችን እንዲሁም በፕሮጀክቱ እየተሳተፋ ያሉ አካላትንም ማበረታታታቸው ተገልጿል።

እንደዚህ አይነት የድጋፍና ክትትል ተግባር በቢሮውና በሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም ዶክተር አሕመዲን መናገራቸውም በመረጃው ተመላክቷል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026