የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>የጋራ አረዳድን በማስረፅና ብሔራዊ ጥቅምን በማስከበር ረገድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና ከፍተኛ ነው</p>

Feb 19, 2025

IDOPRESS

ሰመራ፤ የካቲት 11/2017 (ኢዜአ)፡- የጋራ አረዳድን በማስረፅ ብሔራዊ ጥቅምን በማስከበር እና ቀጣናዊ ትስስርን በማጠናከር ረገድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።

"ብሔራዊ ጥቅሞቻችንና ቀጠናዊ ትስስር ለሚዛናዊ የህዝቦች ተጠቃሚነት" በሚል መሪ ሐሳብ የሠመራ ዩኒቨርሲቲ ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የፓናል ውይይት እየተካሄደ ነው።


የውይይት መድረኩን የከፈቱት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሠላምና የውጭ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባል ወይዘሮ ውበቴ ታደገ እንዳሉት፤ "ዘላቂ ሰላም እና አገራዊ መረጋጋት ሊኖር የሚችለው በጋራ ጉዳዮች ላይ ተቀራራቢ ግንዛቤ ሲኖር ነው"።

እንደ አገር እና ዜጋ የጋራ የሆኑ ህልሞች፣ መገለጫዎች፣ ስጋቶች፣ ጥቅሞችና እሴቶች ያሉን ህዝቦች በመሆናችን የጋራ አረዳድን በማዳበር ብሔራዊ ጥቅሞቻችንን በእያንዳንዱ ዜጋ ውስጥ ማስረፅ አለብን ብለዋል።

ብሔራዊ ጥቅምን ማስጠበቅ የእያንዳንዱ ዜጋ ሃላፊነት መሆኑን ያስገነዘቡት ወይዘሮ ውበቴ፤ በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከፍተኛውን ሚና መጫወት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አገራት ጋር በትብብር በመሥራት በጋራ ለመልማትና ለማደግ እየሠራች መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ቀጠናዊ ትስስርን በማጎልበት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የጎላ ፋይዳ እንዳለውም አብራርተዋል።


በሠመራ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት አብዱራህማን ከድር (ዶ/ር) በበኩላቸው በመድረኩ የአገራችንን ብሔራዊ ጥቅሞች ማስጠበቅና ማስቀጠል በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በጥልቀት ይመከራል ብለዋል።

በፓናል ውይይቱ ላይም በሠላም ሚኒስቴር የብሔራዊ መግባባት ዴስክ ኃላፊ አቶ ገዛኸኝ ጥላሁንን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው መምህራን፣ የአስተዳደር ሰራተኞችና ተማሪዎች እንዲሁም እንግዶች ታድመዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026