የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በመዲናዋ ከጣሪያና ግድግዳ ግብር እስካሁን ከሦስት ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል</p>

Feb 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ በበጀት ዓመቱ ከጣሪያና ግድግዳ ግብር እስካሁን ከሦስት ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች ቢሮ ገለጸ።

በተመሳሳይ በተያዘው በጀት ዓመት ከዚህ በፊት ውዝፍ ዕዳ ከነበረባቸው ባለይዞታዎች ሦስት ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን አሳውቋል።

የቢሮው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለኢዜአ እንዳሉት የጣራና የግድግድ ግብር በየዓመቱ ከሐምሌ እስከ የካቲት 30 ድረስ ያለ ቅጣት ይከፈላል።

በዚህም ከሃምሌ ወር ጀምሮ እስካሁን መክፈል ከሚጠበቅባቸው 429 ሺህ 829 ባለይዞታዎች መካከል እስካሁን 246 ሺህ 725 ባለይዞታዎች ወይም 62 በመቶዎቹ ከፍለዋል ብለዋል።

ግዴታቸውን ከተወጡ ባለይዞታዎች ከ3 ቢሊየን 60 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገልጸዋል።

የጣሪያና ግድግዳ ግብርን በወቅቱ የመክፈል ልምድ እየተሻሻለ መምጣቱን ገልጸው፤ ግብራቸውን በወቅቱ ያልከፈሉ ባለይዞታዎች የካቲት 30 ከመጠናቀቁ በፊት ግዴታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

ግዴታቸውን በወቅቱ በማይወጡ ግብር ከፋዮች ላይ በየወሩ እየጨመረ የሚሄድ የአምስት በመቶ ቅጣት እንደሚጣል ተናግረዋል።

ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2016 ዓ. ም የጣራና ግድግዳ ግብር ያልከፈሉ ግብር ከፋዮች ውዝፍ ዕዳቸውን እየከፈሉ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት የጣሪያና ግድግዳ ግብር ውዝፍ ዕዳ ከሶስት ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.