
አዲስ አበባ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ በበጀት ዓመቱ ከጣሪያና ግድግዳ ግብር እስካሁን ከሦስት ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች ቢሮ ገለጸ።
በተመሳሳይ በተያዘው በጀት ዓመት ከዚህ በፊት ውዝፍ ዕዳ ከነበረባቸው ባለይዞታዎች ሦስት ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን አሳውቋል።
የቢሮው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለኢዜአ እንዳሉት የጣራና የግድግድ ግብር በየዓመቱ ከሐምሌ እስከ የካቲት 30 ድረስ ያለ ቅጣት ይከፈላል።
በዚህም ከሃምሌ ወር ጀምሮ እስካሁን መክፈል ከሚጠበቅባቸው 429 ሺህ 829 ባለይዞታዎች መካከል እስካሁን 246 ሺህ 725 ባለይዞታዎች ወይም 62 በመቶዎቹ ከፍለዋል ብለዋል።

ግዴታቸውን ከተወጡ ባለይዞታዎች ከ3 ቢሊየን 60 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገልጸዋል።
የጣሪያና ግድግዳ ግብርን በወቅቱ የመክፈል ልምድ እየተሻሻለ መምጣቱን ገልጸው፤ ግብራቸውን በወቅቱ ያልከፈሉ ባለይዞታዎች የካቲት 30 ከመጠናቀቁ በፊት ግዴታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
ግዴታቸውን በወቅቱ በማይወጡ ግብር ከፋዮች ላይ በየወሩ እየጨመረ የሚሄድ የአምስት በመቶ ቅጣት እንደሚጣል ተናግረዋል።
ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2016 ዓ. ም የጣራና ግድግዳ ግብር ያልከፈሉ ግብር ከፋዮች ውዝፍ ዕዳቸውን እየከፈሉ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት የጣሪያና ግድግዳ ግብር ውዝፍ ዕዳ ከሶስት ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ጠቁመዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026