የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በአማራ ክልል በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከ510 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ተሸጋግረዋል - የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

ባህርዳር፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ባለፉት ሶስት ዓመታት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በመታገዝ ከ510 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሀላፊ አቶ እንድሪስ አብዱ ገለጹ።

የክልሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የነባርና አዲስ ፕሮጀክቶች የአፈጻጸም ሁኔታ ግምገማና በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ውይይት በባህር ዳር ከተማ ዛሬ አካሂዷል።

በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የቢሮ ሀላፊው አቶ እንድሪስ አብዱ እንደገለጹት ክልሉ በስድስት የልማት ቀጠናዎች እንዲለማና በየአካባቢው ያሉ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ሀብቶች ወደ ስራ እንዲገቡ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።


በተለይ አምራች ኢንዱስትሪውን ለማበረታታት ሲባል የክልሉ መንግስት በክልሉ ዋና ዋና ከተሞች ከ3 ሺህ 260 ሄክታር በላይ መሬት በኢንዱስትሪ ዞንነት በመከለልና ከ27 በላይ የኢንዱስትሪ መንደሮችን በማደራጀት አልሚ ባለሃብቶችን ለመሳብ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የመሬት ዝግጅት ብቻ ሳይሆን አስፈላጊ መሰረተ ልማቶችን በማሟላትና ማነቆዎችን የመፍታት ስራ መከናወኑንም አስረድተዋል።

በመሆኑም በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ ሰፊ መነቃቃት እየተፈጠረ መምጣቱን ገልጸው ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ድረስ ከ510 በላይ አነስተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች በአዲስ ወደ ማምረት ገብተዋል ብለዋል።

በዚህ በጀት ዓመት ብቻ ከ111 በላይ ኢንዱስትሪዎች ምርት እንዲጀምሩ መደረጉን ገልጸው ምርት መጀመር ብቻ ሳይሆን በተለይ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በማረጋገጥና ተኪ ምርቶችን በማምረት አበረታች ስራ መከናወኑን አስረድተዋል።

የወጪ ምርቶችን በማምረትና ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር አምራች ኢንዱስትሪው ሚናው የጎላ መሆኑንም ገልጸዋል።

በተለይም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ ሰፊ መነቃቃት መታየቱን ጠቁመው በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለው ጤናማ ፉክክር እየጨመረ መምጣቱ የማምረት አቅማቸውም እያደገ ነው ብለዋል።

አቶ እንድሪስ እንደገለጹት ከ2014 ዓ.ም ወዲህ እስካሁን ባለው የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ወደ 59 ነጥብ 2 በመቶ ማደጉን ገልጸዋል።


የክልሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብርሃኑ ጣምያለው በበኩላቸው በዚህ አመት በማምረቻ ዘርፉ ከ80 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት ምርት ተመርቷል ብለዋል።

ኢንዱስትሪዎቹ እየሄዱበት ያለው እንቅስቃሴ ጥሩ መሆኑን ገልጸው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት በኩል የድርሻቸውን እየተወጡ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

በመድረኩ የክልሉ የዘርፉ ከፍተኛ አሠራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026