የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በቀጣይ የፆም ወራት የቅዳሜና እሁድ ገበያ ሳምንቱን ሙሉ ይደረጋል- ሐረሪ ክልል</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ የካቲት 14/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል የቀጣይ የዐቢይና ረመዳን ጾሞችን ተከትሎ የምርትና ሸቀጥ አቅርቦት ለመጨመር የቅዳሜና እሁድ ገበያ ከእሁድ እስከ እሁድ እንደሚቀጥል የክልሉ ንግድ ልማት ኤጀንሲ ገለፀ።

በክልሉ መጪዎቹ የፆም ወራት የምርትና ሸቀጥ እጥረት እና የዋጋ ጭማሪ እንዳይከሰት ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑም ተገልጿል።

በክልሉ ንግድ ልማት ኤጀንሲ የንግድ ምዝገባ፣ ፍቃድና ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ ሚሊዮን ጽጌ ለኢዜአ እንዳሉት በክልሉ የዐብይ እና ረመዳን ፆም ወራት በገበያ ላይ የምርትና የሸቀጥ እጥረት እና የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እየተሰራ ነው።

የቅዳሜና እሁድ ገበያ የተረጋጋ የገበያ መፍጠሩን ጠቅሰው፤ በዚህም በቀጣይ የፆሙ ወራት ከእሁድ እስከ እሁድ እንደሚደረግ ጠቁመዋል።

የሸቀጦች ዋጋን ለመቆጣጠር ግብረ ሃይል ተቋቁሞ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለአብነትም በዘይት ምርት ከመሸጫ ዋጋ ተመን ወጭ ጭማሪ ያደረጉ 10 የንግድ ተቋማት እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል።

በግብርና ምርቶችና ሸቀጦች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ ገበያው እንዳይረጋጋ የሚያደርጉ አካላት ላይ ኤጀንሲው የሚያከናውነውን ሕጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026