የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በቀጣይ የፆም ወራት የቅዳሜና እሁድ ገበያ ሳምንቱን ሙሉ ይደረጋል- ሐረሪ ክልል</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ የካቲት 14/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል የቀጣይ የዐቢይና ረመዳን ጾሞችን ተከትሎ የምርትና ሸቀጥ አቅርቦት ለመጨመር የቅዳሜና እሁድ ገበያ ከእሁድ እስከ እሁድ እንደሚቀጥል የክልሉ ንግድ ልማት ኤጀንሲ ገለፀ።

በክልሉ መጪዎቹ የፆም ወራት የምርትና ሸቀጥ እጥረት እና የዋጋ ጭማሪ እንዳይከሰት ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑም ተገልጿል።

በክልሉ ንግድ ልማት ኤጀንሲ የንግድ ምዝገባ፣ ፍቃድና ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ ሚሊዮን ጽጌ ለኢዜአ እንዳሉት በክልሉ የዐብይ እና ረመዳን ፆም ወራት በገበያ ላይ የምርትና የሸቀጥ እጥረት እና የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እየተሰራ ነው።

የቅዳሜና እሁድ ገበያ የተረጋጋ የገበያ መፍጠሩን ጠቅሰው፤ በዚህም በቀጣይ የፆሙ ወራት ከእሁድ እስከ እሁድ እንደሚደረግ ጠቁመዋል።

የሸቀጦች ዋጋን ለመቆጣጠር ግብረ ሃይል ተቋቁሞ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለአብነትም በዘይት ምርት ከመሸጫ ዋጋ ተመን ወጭ ጭማሪ ያደረጉ 10 የንግድ ተቋማት እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል።

በግብርና ምርቶችና ሸቀጦች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ ገበያው እንዳይረጋጋ የሚያደርጉ አካላት ላይ ኤጀንሲው የሚያከናውነውን ሕጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026