የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በክልሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት የተገኙ ስኬቶችን ማስቀጠል ይገባል -- በአሶሳ የከንፍረንሱ ተሳታፊዎች</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

አሶሳ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት የተገኙ ስኬቶችን ማስቀጠል ይገባል ሲሉ በአሶሳ ከተማ በተካሄደው የህዝብ ኮንፍረንስ የተሳተፉ የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ።

በአሶሳ ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት አገር አቀፍ የህዝብ ኮንፍረንስ ተካሂዷል።


በኮንፍረንሱ ላይ አስተያየታቸውን ከሰጡት ነዋሪዎች መካከል አቶ ራህመተላ ታጀሲር፤ በአካባቢው የነበረውን የፀጥታ ችግር የክልሉ መንግስት ከህብረተሰቡ ጋር የፈታበት መንገድ የሚበረታታ ነው።

''የክልሉ መንግሥት ለጀመራቸው የልማት ሥራዎች አጋርነታችንን እንቀጥላለን'' ያሉት አስተያየት ሰጪ የተጀመሩ መልካም ስራዎች መጠናከር አለባቸው ብለዋል።

በቀጣይ በክልሉ የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲሁም ትራንስፖርት አገልግሎት ተደራሽነት ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባም አንስተዋል።


ወይዘሮ ነበሩ ጨርቆሴ በበኩላቸው መንግስት ያመጣቸው የልማት ኢንሼቲቮች በመተግበር ላይ መሆናቸውን ገልጸው፤ ይኸም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

ከአጎራባች ኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች ጋር ያለውን አብሮነት በማጠናከር በክልሉ የተገኘውን ሰላም ማስቀጠል እንደሚገባ የተናገሩት ደግሞ የሀገር ሽማግሌው ሼህ ኢብራሂም ሲራጅ ናቸው።


የአሶሳ ከተማ የስታዲየም ግንባታን ጨምሮ የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እንደሚገባም አስተያየት ሰጪዎቹ ተናግረዋል።

ህዝባዊ ኮንፍረንሱን የመሩት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፤ ለውጡ አዳዲስ ድሎች እንዲመዘገቡ ያደረገ ነው ብለዋል።


ህብረተሰቡ የሚያነሳቸው የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሀገሪቱን የኢኮኖሚ አቅምን የሚያጠናክር ክልል መሆኑን የገለፁት ሚኒስትሯ፤ ይህም ለክልሉ ህዝብ መልካም አጋጣሚ እንደሆነ አክለዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር በበኩላቸው የተነሱ አስተያየቶች ትክክለኛ እና በፓርቲው አቅጣጫዎች ላይ የተቀመጡ ናቸው ብለዋል።


ለልማትና መልካም አስተዳደር ችግሮች ምላሽ ለመስጠት የተያዙት ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች የብልጽግና ጉዞ የሚያሳኩ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።

በመድረኩ ላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026