የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት አካታች የፋይናንስ ሥርዓትን ለመገንባት ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው</p>

Feb 25, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 17/2017(ኢዜአ)፦ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ለአካታች የፋይናንስ ሥርዓት ግንባታና ለሀገራዊ የኢኮኖሚ እድገት አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትና ባንኮች ገለጹ።

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ ከወለድ ነፃ ፋይናንስ ኮንፍረንስ እና ሽልማት መርሐግብር በአዲስ አበባ ተካሂዷል።


የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሥራ አስኪያጅ ሃጅ ካሚል ሀሩን፥ ለዜጎች አማራጭና አካታች የፋይናንስ ስርዓትን ለመገንባት ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎት መጀመሩን አውስተዋል።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት ለአካታች የፋይናንስ ሥርዓት በተሰጠው ትኩረት ሙሉ ለሙሉ ከወለድ ነፃ አገልግሎት የሚሰጡ ባንኮች መከፈታቸውንም ተናግረዋል።

ይህም የለውጡ መንግሥት ለአካታች ፋይናንስ ሥርዓት መጎልበት የሰጠውን ትኩረት ያመላክታል ብለዋል።


የኮንፈረንሱ አስተባባሪ አቶ ነብዩ ሁሴን በኮንፈረንሱ ላይ በርካታ የሀገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማት እንዲሁም የሶማሊያ፣ የጅቡቲና የሱዳን የፋይናንስ ተቋማት መሳተፋቸውን ገልጸዋል፡፡

መርሐ ግብሩ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ዘርፍ ውስጥ ያሉ ሰፊ እድሎችና ልምዶችን መቀመር የተቻለበት እንዲሁም በዘርፉ የላቀ አፈጻጸምና ክንውን ላስመዘገቡ የፋይናንስ ተቋማት እውቅና የተሰጠበት ነው ብለዋል።

በቀጣይ በመላው ዓለም ያሉ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን በማካተት ኮንፈረንሱና የሽልማት መርሐግብሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል።


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲቢኢ ኑር ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኑሪ ሁሴን በበኩላቸው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት አካታች ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ ከፍተኛ ሚና አለው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክም የሲቢኢ ኑር አገልግሎትን ለደንበኞች ተደራሽ እያደረገ ነው ብለዋል።

በዚህም ዜጎች ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እና ለሀገራቸው የኢኮኖሚ ዕድገት በንቃት እንዲሳተፉ እያድረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።


በሲንቄ ባንክ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አወል ዝናቡ፥ ባንኩ የሸሪአ ህግን መሰረት በማድረግ ሲንቄ ኢሳን በሚል ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ባንኩ አገልግሎቱን ለመደበኛ የባንክ ደንበኞችና ለአነስተኛ መካከለኛ የቢዝነስ ተቋማት ተደራሽ በማድረግ ለአካታች ሀገራዊ ልማት አስተዋፅኦ እያደረገ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026