የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያለውን እምቅ ሃብት በማልማት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ ነው</p>

Feb 25, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ የካቲት 17/2017(ኢዜአ):- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያለውን እምቅ ሃብት በማልማት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ።

በአሶሳ ዞን ዑራ ወረዳ በኦሮሚያ ክልል መንግሥት ድጋፍ የተገነባውን የባሮ ኢፈ ቦሩ ትምህርት ቤት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሐሰን ተመርቋል።


በተመሳሳይ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል አሶሳ ከተማ በግል ባለሃብት የተገነባው የምግብ ዘይት ፋብሪካም ተመርቆ ስራ ጀምሯል።

ከዚሁ መርሃ ግብር በኋላ መልዕክት ያስተላለፉት አቶ ሽመልስ አብዲሳ፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያለውን እምቅ ሃብት በማልማት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተደረገ ያለው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።

ለአልሚ ባለሃብቶች በክልሉ በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች መሳተፋቸውም የሚበረታታ ነው ብለዋል።

ከዚሁ መርሃ ግብር በተጨማሪ በአሶሳ የተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር የሌማት ትሩፋት ስራዎችንም ጎብኝተዋል።


የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሐሰን በክልሉ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ ገና ያልተነካ እምቅ ሃብት በመኖሩ ባለሃብቶች በተለያዩ የልማትና ኢንቨስትመንት መስኮች ቢሳተፉ ተጠቃሚ እንደሚሆኑም አንስተዋል።


በዛሬው እለት የተመረቀው የምግብ ዘይት ፋብሪካም ለዚሁ ጥሩ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰው የግብርና ምርቶችን በማቀነባበር እሴት ጨምሮ ለገበያ ማቅረብ የሚያስችል ነው ብለዋል።

በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት በማልማት ህዝቡ ተጠቃሚ እንዲሆን የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠው በክልሉ መስራት የሚፈልጉ ባለሃብቶችን ለመቀበል ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁነት መኖሩንም አረጋግጠዋል።


የፋብሪካው ባለቤት ወይዘሮ ሮማን ፍቃዱ፤ ክልሉ ላደረገላቸው ትብብር አመስግነው በቀጣይም በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች ለመሰማራት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።

የምግብ ዘይት ፋብሪካው በ150 ሚሊዮን ብር የተገነባ ሲሆን የኑግ ምርትን በመጠቀም በብዛት ዘይት በማምረት ለአካባቢው ገበያና ለአጎራባች ክልሎች ጭምር ማቅረብ የሚያስችል መሆኑ ገልጸዋል።

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ በአሶሳ የሌማት ትሩፋት ስራዎችንም ተመልክተዋል።

#Ethiopia

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026