አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባካሄደው የልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታው ላይ 27 ባንኮች መሳተፋቸውን ገለፀ።
ባንኮቹ በአማካይ አንድ የአሜሪካን ዶላር ለመግዛት 135 ነጥብ 6185 ብር ማቅረባቸውን ገልጿል።
ብሔራዊ ባንክ በልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታው ላይ በርካታ ባንኮች መሳተፋቸው መልካም የሚባል መሆኑን አመልክቷል።
በቀጣይ ጊዜ የውጭ ምንዛሪ ገበያ ሁኔታን በቅርበት በመከታተል እንደ አስፈላጊነቱ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሪ ሽያጮችን እንደሚያካሂድ አስታውቋል።
ባንኩ በነሐሴ ወር 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ የልዩ ውጪ ምንዛሬ ጨረታ ማካሄዱ የሚታወስ ነው።