የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ 27 ባንኮች ተሳተፉ</p>

Feb 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባካሄደው የልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታው ላይ 27 ባንኮች መሳተፋቸውን ገለፀ።

ባንኮቹ በአማካይ አንድ የአሜሪካን ዶላር ለመግዛት 135 ነጥብ 6185 ብር ማቅረባቸውን ገልጿል።


ብሔራዊ ባንክ በልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታው ላይ በርካታ ባንኮች መሳተፋቸው መልካም የሚባል መሆኑን አመልክቷል።

በቀጣይ ጊዜ የውጭ ምንዛሪ ገበያ ሁኔታን በቅርበት በመከታተል እንደ አስፈላጊነቱ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሪ ሽያጮችን እንደሚያካሂድ አስታውቋል።

ባንኩ በነሐሴ ወር 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ የልዩ ውጪ ምንዛሬ ጨረታ ማካሄዱ የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.