
አዲስ አበባ ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የመንግስት እና የግል አጋርነትን መፍጠርን ጨምሮ ለቤቶች ልማት የሚያስፈልገውን አማራጭ የፋይናንስ ምንጮች በጥናት መለየቱን አስታወቀ።
በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲግንስ ስር ያሉ ተቋማት የግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸም ግምገማ መካሄዱን እንደቀጠለ ነው።
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የስድስት ወራት አፈጻጸም ቀርቦ ግምግማ ተደርጎበታል።
ኮርፖሬሽኑ በገቢ አሰባሰብ፣ በቤት አቅርቦት፣ የቤቶች ጥገና እና ለግንባታዎች አስፈላጊውን ፋይናንስ በመመደብ ረገድ የላቀ አፈጻጸም ማስመዘገቡ ተመላክቷል።
በግምገማው እንደቀረበው ኮርፖሬሽኑ አፈጻጸሙን ይበልጥ ለማላቅ የንብረት እና ሀብት አስተዳደር አቅሙን ለማሳደግ እቅድ ይዟል።
ለዚህም የኪራይ ሊዝ ስምምነቶች እና የውል አስተዳደር ላይ ትኩረቱን አድርጎ እንደሚሰራ ገልጿል።
በተጨማሪም ኮርፖሬሽኑ በቀጣይ ስድስት ወራት ትኩረት የሚያደርግባቸው የስትራተጂ ትኩረት አቅጣጫዎችንም ለይቷል።
በሪል ስቴቶች ውስጥ ገቢ አመንጪ የሆኑ ንብረቶችን በባለቤትነት መያዝ እና ማስተዳደር፣ የመንግስት እና የግል አጋርነት እንዲሁም ሽርክናን ጨምሮ ለቤቶች ልማት የሚያስፈልጉ አማራጭ የፋይናንስ ሀብቶችን ማፈላለግ ላይ በትኩረት ለመስራት ማቀዱን ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲግንስ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026