የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>ውስብስብና ዓለም አቀፍ ችግሮችን ለመፍታት የተለወጠ የዓለም ስርዓት ያስፈልጋል - አቶ ማሞ ምህረቱ</p>

Feb 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ውስብስብና ዓለም አቀፍ ችግሮችን ለመፍታት የተለወጠ የዓለም ስርዓት ያስፈልጋል ሲሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ ገለጹ።

የብሪክስ አባል ሀገራት ዋና አስተባባሪዎች እና ምክትል አስተባባሪዎች (ሼርፓስ እና ሱስ ሼርፓስ) የ2025 የመጀመሪያ ስብስባ ዛሬ በብራዚል መዲና ብራዚሊያ መካሄድ ጀምሯል።

በአቶ ማሞ ምህረቱ የተመራው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በስብስባው ላይ እየተሳተፈ ነው።


በስብስባው መክፈቻ ላይ የብራዚል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማውሮ ቪዬራ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።

በብሪክስ የኢትዮጵያ ዋና አስተባባሪ (ሼርፓ) አቶ ማሞ ምህረቱ ኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስርዓትን ማዕከል ባደረገ መልኩ ለባለብዙወገን ትብብር እና ለጋራ ደህንነት ድጋፍ ማድረጓን ገልጸዋል።

ለዓለም በርካታ እና ውስብስብ ፈተናዎች መፍትሄ የሆኑ እርምጃዎችን ለመውሰድ የዓለም ስርዓት ከወቅቱ ጋር የሚሄድ ማሻሻያ እንደሚያስፈልገው አመልክተዋል።

አቶ ማሞ ኢትዮጵያ የአዲሱ ልማት ባንክ አባል መሆን በ2025 ቁልፍ የትኩረት መስኮች አንዱ መሆኑን ነው የገለጹት።

በብሪክስ ሀገራት መካከል ያለው የንግድ ግንኙነት አድማስ እንዲሰፋ መስራት እንደሚገባም አመልክተዋል።

በብሪክስ ማዕቀፍ ውስጥ ያሉ ግቦች፣ ፕሮግራሞች እና ኢኒሼቲቮች ትግበራ ውጤታማነት በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል።

በውይይቱ ላይ ኢትዮጵያ ብራዚል በ2025 የብሪክስ ፕሬዝዳንቷ ትኩረት ሰጥታ የምትሰራባቸውን ቁልፍ ጉዳዮች እንደምትደግፍ ገልጻለች።

የዓለም ጤና፣ የዓለም አስተዳደር ስርዓት ማሻሻያ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስ፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት አስተዳደር፣ የደቡባዊ ንፍቀ ክበብ ትብብር እና የብሪክስ የተቋማት ልማት የትኩረት መስኮቹ ናቸው።

የብሪክስ አባል ሀገራት ዋና አስተባባሪዎች እና ምክትል አስተባባሪዎች ስብስባ ለሁለት ቀናት እንደሚቆይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.