
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር የሴት ነጋዴዎች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ትልቅ ኃላፊነት አለበት ሲሉ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።
መንግስት ለማህበሩ ስራዎች ድጋፍ እንደሚያደርግም ተናግረዋል።

የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር የቦርድ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።
ውይይቱ በሴቶች የንግድ እንቅስቃሴ እና ተሳትፎ ላይ ያተኮረ መሆኑን ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
ማህበሩ ህጋዊ መሰረት በመያዝ የሁሉም ክልልና ከተማ አስተዳደር ተወካዮችን ባካተተ መልኩ በአዲስ መልክ መደራጀቱ መልካም የሚባል እርምጃ መሆኑን አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ሴት ነጋዴዎች በሀገር አቀፍ፣ አህጉርና አለም አቀፍ መድረኮች ላይ ያላቸው ተሳትፎ ማሳደግ እና ጠንካራ ተወዳዳሪ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ማህበሩ ሴት ነጋዴዎች እየተከፈቱ ባሉ አዳዲስ የንግድና ገበያ ዕድሎች ውስጥ በመሳተፍ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንዲያረጋግጡ ትልቅ ኃላፊነት አለበት ነው ያሉት ሚኒስትሩ።
በተለይም በአነስተኛ የንግድ ስራ ላይ ተሰማርተው እየተጉ ያሉ ሴቶችን በማብቃት የሴቶችን የተሳትፎ መሰረት ማስፋት እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።
የሴቶች ተሳትፎ ለአካታች ኢኮኖሚና ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ነው ያሉት ሚኒስትሩ በዚህ ረገድም ሚኒስቴሩ ለማህበሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026