
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር የሴት ነጋዴዎች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ትልቅ ኃላፊነት አለበት ሲሉ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።
መንግስት ለማህበሩ ስራዎች ድጋፍ እንደሚያደርግም ተናግረዋል።

የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር የቦርድ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።
ውይይቱ በሴቶች የንግድ እንቅስቃሴ እና ተሳትፎ ላይ ያተኮረ መሆኑን ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
ማህበሩ ህጋዊ መሰረት በመያዝ የሁሉም ክልልና ከተማ አስተዳደር ተወካዮችን ባካተተ መልኩ በአዲስ መልክ መደራጀቱ መልካም የሚባል እርምጃ መሆኑን አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ሴት ነጋዴዎች በሀገር አቀፍ፣ አህጉርና አለም አቀፍ መድረኮች ላይ ያላቸው ተሳትፎ ማሳደግ እና ጠንካራ ተወዳዳሪ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ማህበሩ ሴት ነጋዴዎች እየተከፈቱ ባሉ አዳዲስ የንግድና ገበያ ዕድሎች ውስጥ በመሳተፍ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንዲያረጋግጡ ትልቅ ኃላፊነት አለበት ነው ያሉት ሚኒስትሩ።
በተለይም በአነስተኛ የንግድ ስራ ላይ ተሰማርተው እየተጉ ያሉ ሴቶችን በማብቃት የሴቶችን የተሳትፎ መሰረት ማስፋት እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።
የሴቶች ተሳትፎ ለአካታች ኢኮኖሚና ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ነው ያሉት ሚኒስትሩ በዚህ ረገድም ሚኒስቴሩ ለማህበሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026