የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>ባለፉት ስድስት ወራት የግብርና ልማትን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ከፍተኛ ስኬት ተመዝግቧል</p>

Feb 27, 2025

IDOPRESS

ሐዋሳ፤የካቲት 19/2017 (ኢዜአ):-በክልሉ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት የግብርና ልማትን ጨምሮ በከተማ ልማትና ሌሎችም ዘርፎች ከፍተኛ ስኬት የተመዘገበ መሆኑን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።


የሲዳማ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን በሀዋሳ ከተማ በዛሬው እለት ያካሄደ ሲሆን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶችን የስድስት ወራት አጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ፥ በክልሉ በመስኖ ልማት፣በሌማት ትሩፋት፣የከተማ ልማት እንዲሁም በእንስሳት ልማት ዘርፍና አጠቃላይ በግብርና ልማት የተከናወኑ ተግባራት ትልቅ ስኬት የተመዘገበባቸው መሆኑን አንስተዋል።


ከዚህም በተጨማሪ የቤተሰብ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በ8 ኢኒሼቲቮችና በ68 ፓኬጆች የያዘ ዕቅድ ተግባራዊ በማድረግ ወደ ስራ እንደተገባም ገልጸዋል።


በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመለየት መፍትሄ ለመሻት የክልሉ መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራቱን ጠቅሰው፥ ገበያን በማረጋጋት የኑሮ ውድነቱን ለማቃለልም ብዙ ርቀት መኬዱን ተናግረዋል።


የእንስሳት እርባታና ሌሎች የግብርና ስራዎች ላይ በማተኮር የተከናወነው ስራም ውጤታማ መሆኑን አንስተዋል።


በገቢ አሰባሰብ ረገድም በስድስት ወራት ለመሰብሰብ ከታቀደው 97 በመቶ ማሳካት ተችሏል ብለዋል።


በከተማና በገጠር መንገድ ተደራሽነት፣በኮሪደር ልማትና በመጠጥ ውሃ አቅርቦትም የተያዘው እቅድ የተሳካበት ነው ብለዋል።


የምክር ቤቱ ስብሰባ በዛሬ ውሎው የርዕሰ መስተዳድሩን ሪፖርት ካደመጠ በኋላ አፈጻጸሙን የገመገመ ሲሆን በነገው እለትም የተለያዩ አዋጆችን እንዲሁም ሹመቶችን በማፅደቅ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026