የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>ባለፉት ስድስት ወራት የግብርና ልማትን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ከፍተኛ ስኬት ተመዝግቧል</p>

Feb 27, 2025

IDOPRESS

ሐዋሳ፤የካቲት 19/2017 (ኢዜአ):-በክልሉ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት የግብርና ልማትን ጨምሮ በከተማ ልማትና ሌሎችም ዘርፎች ከፍተኛ ስኬት የተመዘገበ መሆኑን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።


የሲዳማ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን በሀዋሳ ከተማ በዛሬው እለት ያካሄደ ሲሆን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶችን የስድስት ወራት አጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ፥ በክልሉ በመስኖ ልማት፣በሌማት ትሩፋት፣የከተማ ልማት እንዲሁም በእንስሳት ልማት ዘርፍና አጠቃላይ በግብርና ልማት የተከናወኑ ተግባራት ትልቅ ስኬት የተመዘገበባቸው መሆኑን አንስተዋል።


ከዚህም በተጨማሪ የቤተሰብ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በ8 ኢኒሼቲቮችና በ68 ፓኬጆች የያዘ ዕቅድ ተግባራዊ በማድረግ ወደ ስራ እንደተገባም ገልጸዋል።


በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመለየት መፍትሄ ለመሻት የክልሉ መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራቱን ጠቅሰው፥ ገበያን በማረጋጋት የኑሮ ውድነቱን ለማቃለልም ብዙ ርቀት መኬዱን ተናግረዋል።


የእንስሳት እርባታና ሌሎች የግብርና ስራዎች ላይ በማተኮር የተከናወነው ስራም ውጤታማ መሆኑን አንስተዋል።


በገቢ አሰባሰብ ረገድም በስድስት ወራት ለመሰብሰብ ከታቀደው 97 በመቶ ማሳካት ተችሏል ብለዋል።


በከተማና በገጠር መንገድ ተደራሽነት፣በኮሪደር ልማትና በመጠጥ ውሃ አቅርቦትም የተያዘው እቅድ የተሳካበት ነው ብለዋል።


የምክር ቤቱ ስብሰባ በዛሬ ውሎው የርዕሰ መስተዳድሩን ሪፖርት ካደመጠ በኋላ አፈጻጸሙን የገመገመ ሲሆን በነገው እለትም የተለያዩ አዋጆችን እንዲሁም ሹመቶችን በማፅደቅ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026