
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፡- የዓድዋ ድል እና የህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያን በየዘመናቸው በአብሮነት ያሳኳቸው ዘመን ተሻጋሪ ድሎች ናቸው ሲሉ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) ገለፁ።
ኢትዮጵያውያን በጋራ ተባብረው ለሀገራቸው ዘመን ተሻጋሪና ለሌሎችም አርአያ የሚሆኑ ተግባራትን በመፈጸም እንደቀጠሉ ናቸው።
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) የዓድዋ ድልን እና የዘመኑ የአርበኝነት ተምሳሌት የሆነው የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የአንድነት ተምሳሌት፤ የአይቻልም አስተሳሰብን በማሸነፍ በተግባር ያረጋገጡበት ለመጪው ትውልድ ትልቅ ታሪክ ነው ብለዋል።

መላው ኢትዮጵያውያን ከህፃን እስከ አዋቂ ከሀገር እስከ ውጭ በጋራ ርብርብ ያገባደዱት የዘመናችን አሻራ መሆኑንም ተናግረዋል።
የዓድዋ ድልም ኢትዮጵያውያን በጋራ ሆነው የጸረ ቅኝ ግዛት ትግል በማድረግ ለመላው የአለም ጥቁር ህዝቦች ጭምር ኩራት የሆነ ዘመን ተሻጋሪ ድል እንደሆነ አንስተዋል።
የህዳሴ ግድብንና የዓድዋ ድልን በርካታ የሚያመሳስላቸው ነገሮች እንዳሉ ገልጸው፤ ዓድዋ ኢትዮጵያውያን በወኔ፣ በጀግንነት እና በህብረ ብሔራዊ አንድነት የተጎናጸፉት ድል መሆኑን ጠቅሰዋል።
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብም ኢትዮጵያውያን በራሳቸው የፋይናንስ አቅም አንድነታቸውን በማጠናከር ዘመን ተሻጋሪ ድል አድራጊነትን ያሳዩበት ነው ብለዋል።
የዓድዋ ድል የውጫሌ ስምምነትንና ቀኝ ገዥዎች በጥቁር ህዝቦች ላይ የነበራቸውን ያልተገባ አስተሳሰብ ያሸነፈ መሆኑን ተናግረዋል።
በተመሳሳይ ህዳሴ ግድብም በአባይ ወንዝ ላይ ያዘጋጀናቸውን ሰነዶች በትብብር ማዕቀፍ ስምምነት እና የህዳሴ ግድብን በመገንባት ዳግም ድል የተጎናፀፍንበት ነው ሲሉም ገልፀዋል።
129ኛው የዓድዋ ድል በዓል "ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል" በሚል መሪ ሃሳብ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም ይከበራል፡፡
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026