የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>የዓድዋ ድል እና የህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያን በየዘመናቸው በአብሮነት ያሳኳቸው ዘመን ተሻጋሪ ድሎች ናቸው - ሚኒስትር ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)</p>

Feb 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፡- የዓድዋ ድል እና የህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያን በየዘመናቸው በአብሮነት ያሳኳቸው ዘመን ተሻጋሪ ድሎች ናቸው ሲሉ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) ገለፁ።

ኢትዮጵያውያን በጋራ ተባብረው ለሀገራቸው ዘመን ተሻጋሪና ለሌሎችም አርአያ የሚሆኑ ተግባራትን በመፈጸም እንደቀጠሉ ናቸው።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) የዓድዋ ድልን እና የዘመኑ የአርበኝነት ተምሳሌት የሆነው የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የአንድነት ተምሳሌት፤ የአይቻልም አስተሳሰብን በማሸነፍ በተግባር ያረጋገጡበት ለመጪው ትውልድ ትልቅ ታሪክ ነው ብለዋል።


መላው ኢትዮጵያውያን ከህፃን እስከ አዋቂ ከሀገር እስከ ውጭ በጋራ ርብርብ ያገባደዱት የዘመናችን አሻራ መሆኑንም ተናግረዋል።

የዓድዋ ድልም ኢትዮጵያውያን በጋራ ሆነው የጸረ ቅኝ ግዛት ትግል በማድረግ ለመላው የአለም ጥቁር ህዝቦች ጭምር ኩራት የሆነ ዘመን ተሻጋሪ ድል እንደሆነ አንስተዋል።

የህዳሴ ግድብንና የዓድዋ ድልን በርካታ የሚያመሳስላቸው ነገሮች እንዳሉ ገልጸው፤ ዓድዋ ኢትዮጵያውያን በወኔ፣ በጀግንነት እና በህብረ ብሔራዊ አንድነት የተጎናጸፉት ድል መሆኑን ጠቅሰዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብም ኢትዮጵያውያን በራሳቸው የፋይናንስ አቅም አንድነታቸውን በማጠናከር ዘመን ተሻጋሪ ድል አድራጊነትን ያሳዩበት ነው ብለዋል።

የዓድዋ ድል የውጫሌ ስምምነትንና ቀኝ ገዥዎች በጥቁር ህዝቦች ላይ የነበራቸውን ያልተገባ አስተሳሰብ ያሸነፈ መሆኑን ተናግረዋል።

በተመሳሳይ ህዳሴ ግድብም በአባይ ወንዝ ላይ ያዘጋጀናቸውን ሰነዶች በትብብር ማዕቀፍ ስምምነት እና የህዳሴ ግድብን በመገንባት ዳግም ድል የተጎናፀፍንበት ነው ሲሉም ገልፀዋል።

129ኛው የዓድዋ ድል በዓል "ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል" በሚል መሪ ሃሳብ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም ይከበራል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026