የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በክልሉ ሁለት የገጠር መንገድ ፕሮጀክቶች ተመረቁ</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

ሀላባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን በሀዲያና ሀላባ ዞኖች ከ61 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ያስገነባቸው ሁለት የገጠር መንገድ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ።

መንገዶቹ በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ አሻሹሬ-ሚቶ እና በሀድያ ዞን ጌሜዶ-ሞርሲጦ 29 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ ሁለት የገጠር መንገዶች ከ61 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎባቸዋል ተብሏል።


በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑርዬ (ዶ/ር) እንዳሉት፣ የመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነት የክልሉን ፈጣን እድገት ለማረጋገጥ ያግዛል።

የገጠሩን ማህበረሰቡ የኢኮኖሚ ለማሳደግ የተጀመረውን ጥረት ከግብ ለማድረስ የመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነት ማስፋት ቀዳሚ በመሆኑ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው ብለዋል።

የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ምስጋና ማቲዎስ በበኩላቸው በክልሉ በርካታ የገጠር መንገዶችን በመገንባትና በመጠገን አገልግሎት እንዲሰጡ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በሁለቱ ዞኖች የተመረቁ 29 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ የገጠር መንገዶች ከ61 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መውጣቱን ጠቅሰዋል።

አስተያየታቸውን የሰጡት የአካባቢው ነዋሪዎችም በዕለቱ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የበቁ መንገዶች ዘርፈ ብዙ ችግሮችን እንደሚቀርፍላቸው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026