የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>ሁለተኛው ያልተማከለ የአደጋ አስተዳደር ስጋት ቅነሳ ፕሮጀክት ይፋ ሆነ</p>

Mar 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- ሁለተኛው ያልተማከለ የአደጋ አስተዳደር ስጋት ቅነሳ ፕሮጀክት ይፋ ሆኗል።

የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማሪያም(ዶ/ር) ፕሮጀክቱ ይፋ በሆነበት ወቅት እንደገለጹት፤ ለሁለተኛው ያልተማከለ የአደጋ አስተዳደር ቅነሳ ፕሮጀክት ከአውሮፓ ሕብረት 20 ሚሊዮን ዩሮ ተግባራዊ ይደረጋል።

ለዜጎች የሚሰጡ ሰብዓዊ ድጋፎች ዜጎችን በዘላቂነት ማቋቋም እንዲችሉ እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል።


ፕሮጀክቱ በዘጠኝ ክልሎች ለአራት ዓመታት እንደሚተገበር ጠቁመው፤ ከፕሮጀክቱ በቀጥታና በተዘዋዋሪ አንድ ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ዜጎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።

ባለፉት አራት ዓመታት ተግባራዊ የተደረገው የአውሮፓ ሕብረት ያልተማከለ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ፕሮጀክት ስጋትን በመከላከል ተግባር ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ መቆየቱ ተናግረዋል።

ፕሮጀክቱ ከቤተሰብ ጀምሮ አካባቢና የአካባቢ መዋቅርን አቅም በመፍጠር ለአደጋ ስጋት አይበገሬነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት በአምስት ክልሎች የራሱ አስተዋጽኦ ሲያደርግ መቆየቱን አብራርተዋል።


የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው በበኩላቸው፤ መንግስት አደጋዎችን አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል አቅምን በማሳደግ ረገድ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በዛሬው እለት በይፋ የተጀመረው የአውሮፓ ሕብረት ፕሮጀክት ለአደጋ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ጋር የተጣጣመ ለማድረግ የሚያግዝ ነው።

የአውሮፓ ሕብረትና ሌሎች የልማት አጋር አካላትም አደጋን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት ለኢትዮጵያ ድጋፋቸውን እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

ሕብረቱ ለሁለተኛው ዙር ያልተማከለ የአደጋ አስተዳደር ስጋት ቅነሳ ፕሮጀክት የሰጠው ድጋፍም ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ዜጎችን ለመደገፍ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ እንደሆነ ተናግረዋል።


የአውሮፓ ሕብረት ልዑካን ቡድን የትብብር ኃላፊ ሮቤርቶ ሰኪሎር እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ሕብረት ያልተማከለ የአደጋ ስጋት አስተዳደር ላይ ያሏዋቸው ፖሊሲዎች ተጣጥመው የሚሔዱ ናቸው።

በሁለተኛው ምዕራፍ ፕሮጀክት ቀጥታ የገንዘብ ድጋፍ የተደረገ ሲሆን፤ ባለፉት አራት ዓመታት ተግባራዊ የተደረገው የመጀመሪያው ምዕራፍ ፕሮጀክት ስኬታማ መሆኑን ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026