የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>የአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል የሀገራችንን የንግድ ስርዓት ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው - የንግዱ ማህበረሰብ አባላት</p>

Mar 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 23/2017(ኢዜአ)፡- የአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል የአሀገራችንን የንግድ ስርዓት ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው ሲሉ የአዲስ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከልን ትናንት መርቀው ከፍተዋል።

የአዲስ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አባላት በዛሬው እለት የአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከልን ጎብኝተዋል፡፡

ኢዜአ ካነጋገራቸው የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤቱ አባላት መካከል ወይዘሮ ደስታ ወለጋ፤ ማዕከል የሀገራችንን የንግድ ስርዓት ወደ ተሻለ ምዕራፍ በማሸጋገር የንግድ ማህበረሰቡን ይበልጥ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በመዲናዋ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት ለመጪው ትውልድም የሚተርፉ መሆናቸውን መገንዘባቸውን ገልጸዋል፡፡

ማዕከሉ ኢትዮጵያ ያሏትን ፀጋዎች ለዓለም በማስተዋወቅ የንግድ ስርዓቷን የምታሳድግበት መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሌላኛው የጉብኝቱ ተሳታፊ አቶ ሙሉጌታ መስፍን ናቸው።

በተለይም ከዚህ በፊት እንደ ከተማ የነበሩ የአገልግሎት ጉድለቶችን በመሙላት ቱሪስቶች ወደ ኢትዮጵያ በብዛት እንዲመጡና የቆይታ ጊዜያቸውን እንዲያራዝሙ የሚያድርግ መሆኑን ተናግረዋል።

የአዲስ ኢንተርናስናል ኮንቬንሽን ማዕከል የሀገሪቱን እድገት የሚያሳልጥ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የጉብኝቱ ተሳታፊ ወይዘሪት ሸዋ ጎፋ ናቸው፡፡

በአጭር ጊዜ ይህን ያህል ግዙፍ ማዕከል ተገንብቶ ማየታቸው እጅግ እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል፡፡

ሌላኛው የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤቱ አባል አቶ ሚካኤል ተክሌ በበኩላቸው፤ የማዕከሉ ግንባታ ኢትዮጵያን የቱሪዝም ኮንፍረንስ ማዕከል ማድረግ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

የንግዱ ማህበረሰብን ግንኙነት ይበልጥ በማጠናከር የዘመነ የንግድ ስርዓት እንደዘረጋ እንደሚያግዝም ተናግረዋል፡፡

ማዕከሉ 40 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን፤ እያንዳንዳቸው ከ3 ሺህ እስከ 4 ሺህ ሰዎችን የመያዝ አቅም ያላቸው 2 ትላልቅ አዳራሾች፣ 8 አነስተኛ እና መካከለኛ የመሰብሰቢያ አዳራሾች በጠቅላላ እስከ 10 ሺህ ሰዎችን የሚያስተናግዱ አዳራሾችን የያዘ ነው።

ማዕከሉ ዘመናዊ ሆቴልን፣ ሪስቶራንቶችን፣ ሾው ሩሞችን፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ ለልዩ ልዩ አገልግሎት መስጫ ስፍራዎችን በአንድ ያካተተ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026