
አዲስ አበባ፤ የካቲት 23/2017(ኢዜአ)፡- የአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል የአሀገራችንን የንግድ ስርዓት ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው ሲሉ የአዲስ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከልን ትናንት መርቀው ከፍተዋል።
የአዲስ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አባላት በዛሬው እለት የአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከልን ጎብኝተዋል፡፡
ኢዜአ ካነጋገራቸው የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤቱ አባላት መካከል ወይዘሮ ደስታ ወለጋ፤ ማዕከል የሀገራችንን የንግድ ስርዓት ወደ ተሻለ ምዕራፍ በማሸጋገር የንግድ ማህበረሰቡን ይበልጥ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በመዲናዋ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት ለመጪው ትውልድም የሚተርፉ መሆናቸውን መገንዘባቸውን ገልጸዋል፡፡
ማዕከሉ ኢትዮጵያ ያሏትን ፀጋዎች ለዓለም በማስተዋወቅ የንግድ ስርዓቷን የምታሳድግበት መሆኑን የገለጹት ደግሞ ሌላኛው የጉብኝቱ ተሳታፊ አቶ ሙሉጌታ መስፍን ናቸው።
በተለይም ከዚህ በፊት እንደ ከተማ የነበሩ የአገልግሎት ጉድለቶችን በመሙላት ቱሪስቶች ወደ ኢትዮጵያ በብዛት እንዲመጡና የቆይታ ጊዜያቸውን እንዲያራዝሙ የሚያድርግ መሆኑን ተናግረዋል።
የአዲስ ኢንተርናስናል ኮንቬንሽን ማዕከል የሀገሪቱን እድገት የሚያሳልጥ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የጉብኝቱ ተሳታፊ ወይዘሪት ሸዋ ጎፋ ናቸው፡፡
በአጭር ጊዜ ይህን ያህል ግዙፍ ማዕከል ተገንብቶ ማየታቸው እጅግ እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል፡፡
ሌላኛው የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤቱ አባል አቶ ሚካኤል ተክሌ በበኩላቸው፤ የማዕከሉ ግንባታ ኢትዮጵያን የቱሪዝም ኮንፍረንስ ማዕከል ማድረግ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
የንግዱ ማህበረሰብን ግንኙነት ይበልጥ በማጠናከር የዘመነ የንግድ ስርዓት እንደዘረጋ እንደሚያግዝም ተናግረዋል፡፡
ማዕከሉ 40 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን፤ እያንዳንዳቸው ከ3 ሺህ እስከ 4 ሺህ ሰዎችን የመያዝ አቅም ያላቸው 2 ትላልቅ አዳራሾች፣ 8 አነስተኛ እና መካከለኛ የመሰብሰቢያ አዳራሾች በጠቅላላ እስከ 10 ሺህ ሰዎችን የሚያስተናግዱ አዳራሾችን የያዘ ነው።
ማዕከሉ ዘመናዊ ሆቴልን፣ ሪስቶራንቶችን፣ ሾው ሩሞችን፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ ለልዩ ልዩ አገልግሎት መስጫ ስፍራዎችን በአንድ ያካተተ ነው፡፡
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026