የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በክልሉ በግብርና ልማት ሥራ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ገቢን ለማሳደግ እየተሰራ ነው</p>

Mar 4, 2025

IDOPRESS

መቱ፤ የካቲት 24/2017 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል የግብርና ልማት ሥራን የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ የአርሶ አደሩን ገቢ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።

የቢሮው ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ በኢሉባቦር ዞን አሌና ቡሬ ወረዳዎች በማር ምርት እና በስንዴ ልማት እየተከናወኑ ያሉ የግብርና ልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።


በዚህ ወቅት ኃላፊው እንደገለጹት በክልሉ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየተከናወኑ ባሉ የግብርና ፕሮግራሞች አርሶ አደሩ ተጠቃሚ መሆን ጀምሯል።

ፕሮግራሞቹን ይበልጥ በማስፋፋት አርሶ አደሩ የምግብ ዋስትናውን ከማረጋገጥ ባለፈ ምርቶቹን ወደውጭ ልኮ ገቢውን እንዲያሳድግ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

"በግብርና ልማት ትኩረት ከተሰጣቸው አንዱ የማር ምርትና ምርታማነትን መጨመር ነው" ያሉት አቶ ጌቱ በመስኩ የተያዘውን ግብ ለማሳካት በተያዘው ዓመት 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዘመናዊ ቀፎዎችን ለአርሶ አደሩ ለማሰራጨት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ጠቅስዋል።

በዞኑ ቡሬ ወረዳ ነቦ ምሪጋ ቀበሌ በኩታ ገጠም እየለማ ያለው የስንዴ ልማትም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አቶ ጌቱ ተናግረዋል።

ከሀገራዊ ለውጡ በፊት በኢሉባቦር ዞን 240 ዘመናዊ ቀፎዎች ብቻ እንደነበሩ ያስታወሱት ደግሞ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ ናቸው።


"ከለውጡ ወዲህ መንግስት ለግብርና ዘርፍ በሰጠው ትኩረትና በተሰራው ሥራ በአሁኑ ወቅት 340 ሺህ ዘመናዊ ቀፎዎችን ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ ተችሏል" ብለዋል።

በተያዘው ዓመት 16 ሺህ ቶን ማር ለማምረትና ምርቱንም ለውጭ ገበያ ማቅረብ እንደ አንድ ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን አክለዋል።

እንደ እሳቸው ገለጻ በዞኑ በተያዘው የበጋ ወቅት 96 ሺህ ሄክታር መሬት በስንዴ ሰብል እየለማ ይገኛል።

በአሌ ወረዳ በንብ ማነብ ሥራ የተሰማሩት አቶ ታከለ ማሞ 140 ዘመናዊ፣ ባሕላዊና የሽግግር ቀፎዎች እንዳሏቸው ተናግረዋል።

በተሰማሩበት የንብ ማነብ ሥራ ምርታማነታቸውንና ገቢያቸውን በማሳደግ ወደ ኢንቨስትመንት ዘርፍ ለመሸጋገር አቅደው እየሰሩ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በስንዴ ልማት የተሰማሩት የነቦ ምሪጋ ቀበሌ ነዋሪዎችም በበኩላቸው አሁን እየለማ ከሚገኘው ስንዴ ጥሩ ምርት ለማግኘት ተስፋ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026