
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2017(ኢዜአ)፡- ለ2017/18 የምርት ዘመን እስከ አሁን ከ658 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ መጓጓዙን የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ለምርት ዘመኑ ግብዓት የሚሆን 24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዢ ለመፈጸም ታቅዶ እስከ የካቲት 23/2017 ዓ.ም. ድረስ 700 ሺህ 763 ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ ጅቡቲ ወደብ መድረሱን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ጅቡቲ ወደብ ከደረሰው የአፈር ማዳበሪያ መካከልም እስከተጠቀሰው ዕለት ድረስ 658 ሺህ 249 ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ መጓጓዙ ተመላክቷል።
የአፈር ማዳበሪያው በ13 መርከቦች ተጭኖ ጅቡቲ ወደብ ደርሷል።
ወደ ሀገር ውስጥ ከተጓጓዘው ውጭ 42 ሺህ 513 ነጥብ 9 ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ በወደብ ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል።
ወደ አገር ውስጥ ከተጓጓዘው ውስጥ 418 ሺህ 670.2 ሜትሪክ ቶን ዳፕ እንዲሁም 239 ሺህ 579 ሜትሪክ ቶን ደግሞ ዩሪያ የተሰኘው የአፈር ማዳበሪያ አይነት ነው።
ማዳበሪያው በባቡር እና በድንበር ተሻጋሪ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ መጓጓዙን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026