የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>ለምርት ዘመኑ ከ658 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ ተጓጉዟል</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2017(ኢዜአ)፡- ለ2017/18 የምርት ዘመን እስከ አሁን ከ658 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ መጓጓዙን የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ለምርት ዘመኑ ግብዓት የሚሆን 24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዢ ለመፈጸም ታቅዶ እስከ የካቲት 23/2017 ዓ.ም. ድረስ 700 ሺህ 763 ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ ጅቡቲ ወደብ መድረሱን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

ጅቡቲ ወደብ ከደረሰው የአፈር ማዳበሪያ መካከልም እስከተጠቀሰው ዕለት ድረስ 658 ሺህ 249 ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ መጓጓዙ ተመላክቷል።

የአፈር ማዳበሪያው በ13 መርከቦች ተጭኖ ጅቡቲ ወደብ ደርሷል።

ወደ ሀገር ውስጥ ከተጓጓዘው ውጭ 42 ሺህ 513 ነጥብ 9 ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ በወደብ ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል።

ወደ አገር ውስጥ ከተጓጓዘው ውስጥ 418 ሺህ 670.2 ሜትሪክ ቶን ዳፕ እንዲሁም 239 ሺህ 579 ሜትሪክ ቶን ደግሞ ዩሪያ የተሰኘው የአፈር ማዳበሪያ አይነት ነው።

ማዳበሪያው በባቡር እና በድንበር ተሻጋሪ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ መጓጓዙን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026