
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2017(ኢዜአ)፡- ለ2017/18 የምርት ዘመን እስከ አሁን ከ658 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ መጓጓዙን የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ለምርት ዘመኑ ግብዓት የሚሆን 24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዢ ለመፈጸም ታቅዶ እስከ የካቲት 23/2017 ዓ.ም. ድረስ 700 ሺህ 763 ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ ጅቡቲ ወደብ መድረሱን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ጅቡቲ ወደብ ከደረሰው የአፈር ማዳበሪያ መካከልም እስከተጠቀሰው ዕለት ድረስ 658 ሺህ 249 ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ መጓጓዙ ተመላክቷል።
የአፈር ማዳበሪያው በ13 መርከቦች ተጭኖ ጅቡቲ ወደብ ደርሷል።
ወደ ሀገር ውስጥ ከተጓጓዘው ውጭ 42 ሺህ 513 ነጥብ 9 ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ በወደብ ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል።
ወደ አገር ውስጥ ከተጓጓዘው ውስጥ 418 ሺህ 670.2 ሜትሪክ ቶን ዳፕ እንዲሁም 239 ሺህ 579 ሜትሪክ ቶን ደግሞ ዩሪያ የተሰኘው የአፈር ማዳበሪያ አይነት ነው።
ማዳበሪያው በባቡር እና በድንበር ተሻጋሪ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ መጓጓዙን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026