የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>ኮንቬንሽን ማዕከሉ የአገሪቷ ኩራትና የከተማዋ ተጨማሪ ድምቀት ነው</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2017(ኢዜአ)፡-የአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል የአገር ኩራት የከተማዋ ተጨማሪ ድምቀት ነው ሲሉ ማዕከሉን የጎበኙ የተለያዩ ከፌዴራል ተቋማት የተውጣጡ ጎብኚዎች ገለጹ።


የአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከልን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም መርቀው መክፈታቸው ይታወሳል።


ማዕከሉ 40 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን እያንዳንዳቸው ከ 3 ሺህ እስከ 4 ሺህ ሰዎችን የመያዝ አቅም ያላቸው ሁለት ትላልቅ የመሰብሰቢያ አዳራሾችን ይዟል።


ስምንት አነስተኛ እና መካከለኛ የመሰብሰቢያ አዳራሾችን ዘመናዊ ሆቴልን፣ ሪስቶራንቶችን፣ ሾው ሩሞችን፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎችና ሌሎች ልዩ ልዩ አገልግሎት መስጫዎችንም አካቷል፡፡


ይህንን ማዕከል የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጉብኝተውታል።


በጉብኝቱ ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው አስተያየት ሰጪዎች እንደገለጹት፤ በአገሪቷ በርካታ ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ በፍጥነት እየተከናወኑና እየተጠናቀቁ ናቸው።


የአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል ግንባታ ተጠናቆ በመመረቁ እንዳስደነቃቸው ተናግረዋል።


ማዕከሉን ከጎበኙ አስተያየት ሰጪዎች መካከል ቤዛዊት ታምራት፤ ማዕከሉ ለአገር ኩራት ለከተማው ደግሞ ተጨማሪ ድምቀት መሆኑን ገልጻለች፡፡


ማዕከሉ ለአገር ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዳለው አመልክታ፤ ቱሪስቶች እና ኢንቨስተሮችን ለመሳብ የሚያስችል መሆኑን ጠቁማለች።


ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ እናት ካሳ በበኩሏ፤ ማዕከሉ እንዳስደነቃትና በዚህም እጅግ ኩራት እና ደስታ እንደተሰማት ጠቁማለች፡፡


ማዕከሉ የውጪ ምንዛሬ ምንጭ በመሆን ለአገር ኢኮኖሚያዊ እድገት እና ብልጽግና ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ያላትን እምነትም ተናግራለች፡፡


ሌላው ጎብኚ ታዬ ተረፈ በበኩሉ እንደተናገረው፤ የተሰራው ስራ አገርን የሚያኮራ የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያሳድግ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026