የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>ኮንቬንሽን ማዕከሉ የአገሪቷ ኩራትና የከተማዋ ተጨማሪ ድምቀት ነው</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2017(ኢዜአ)፡-የአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል የአገር ኩራት የከተማዋ ተጨማሪ ድምቀት ነው ሲሉ ማዕከሉን የጎበኙ የተለያዩ ከፌዴራል ተቋማት የተውጣጡ ጎብኚዎች ገለጹ።


የአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከልን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም መርቀው መክፈታቸው ይታወሳል።


ማዕከሉ 40 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን እያንዳንዳቸው ከ 3 ሺህ እስከ 4 ሺህ ሰዎችን የመያዝ አቅም ያላቸው ሁለት ትላልቅ የመሰብሰቢያ አዳራሾችን ይዟል።


ስምንት አነስተኛ እና መካከለኛ የመሰብሰቢያ አዳራሾችን ዘመናዊ ሆቴልን፣ ሪስቶራንቶችን፣ ሾው ሩሞችን፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎችና ሌሎች ልዩ ልዩ አገልግሎት መስጫዎችንም አካቷል፡፡


ይህንን ማዕከል የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጉብኝተውታል።


በጉብኝቱ ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው አስተያየት ሰጪዎች እንደገለጹት፤ በአገሪቷ በርካታ ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ በፍጥነት እየተከናወኑና እየተጠናቀቁ ናቸው።


የአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል ግንባታ ተጠናቆ በመመረቁ እንዳስደነቃቸው ተናግረዋል።


ማዕከሉን ከጎበኙ አስተያየት ሰጪዎች መካከል ቤዛዊት ታምራት፤ ማዕከሉ ለአገር ኩራት ለከተማው ደግሞ ተጨማሪ ድምቀት መሆኑን ገልጻለች፡፡


ማዕከሉ ለአገር ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዳለው አመልክታ፤ ቱሪስቶች እና ኢንቨስተሮችን ለመሳብ የሚያስችል መሆኑን ጠቁማለች።


ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ እናት ካሳ በበኩሏ፤ ማዕከሉ እንዳስደነቃትና በዚህም እጅግ ኩራት እና ደስታ እንደተሰማት ጠቁማለች፡፡


ማዕከሉ የውጪ ምንዛሬ ምንጭ በመሆን ለአገር ኢኮኖሚያዊ እድገት እና ብልጽግና ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ያላትን እምነትም ተናግራለች፡፡


ሌላው ጎብኚ ታዬ ተረፈ በበኩሉ እንደተናገረው፤ የተሰራው ስራ አገርን የሚያኮራ የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያሳድግ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026