የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቶችን የቴክኖሎጂ እውቀት በማሳደግ የስራ እድል እየፈጠረ ነው

Mar 10, 2025

IDOPRESS

ደብረ ማርቆስ፤የካቲት 29/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቶችን የቴክኖሎጂ እውቀት በማሳደግ ክህሎታቸው እንዲዳብር በማድረገግ የስራ እድልን ለመፍጠር እንዳገዛቸው የደብረ ማርቆስ ከተማ ወጣቶች ገለጹ።


ወጣቶቹ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ መንግስት ባመቻቸላቸው የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በመሳተፍ ወቅቱ ከሚጠይቀው ቴክኖሎጂ ጋር በመላመድ እጃቸው ላይ ባለው ስልክ መረጃዎችን በማሰስ ለስራ እድል ፈጠራ ማዋል አስችሏል።


የከተማ አስተዳደሩ ስራና ስልጠና መምሪያ ያዘጋጀውን ስልጠናው ወስደው ከተመረቁ ወጣቶች መካከል ትልቅሰው አንሙት እንዳለችው፥ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ከቴክኖሎጂ ጋር እንድትላመድ አድርጓታል።


ስልጠናውን ከመውሰዷ በፊት እጇ ላይ ያለውን ስልክ ከመደወልና ፌስቡክ ከመጠቀም የዘለለ እውቀት እንዳልነበራት አስታውሳ አሁን ባገኘችው ስልጠና የተለያዩ ፕሮግራሞችን በመስራትና መረጃዎችን በመፈለግ ለስራ እድል ፈጠራ ለማዋል እንዳገዛት አስረድታለች።


ወጣት ገነት አበባው በበኩሏ፥ የኮደርስ ስልጠና በቴክኖሎጂ ራሷን ለማብቃትና ተጠቃሚ ለመሆን እንዳገዛት ተናግራለች።


ይህን እድል ሌሎች ወጣቶችም በመጠቀም ራሳቸውን ከቴክኖሎጂው ጋር በማስተዋወቅ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከልምዷ አካፍላለች።


የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አቶ መኮንን ሙሉአዳም ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ቴክኖሎጂን የታጠቀ ማህበረሰብን በመገንባት ዓለም የደረሰበት የእድገት ደረጃን ለማስተካከል እየተሰራ ነው።


በበጀት ዓመቱ ከ3 ሺህ በላይ ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ እስካሁን ከ1 ሺህ 300 በላይ ወጣቶች የእድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።


የታቀደውን የኮደርስ ስልጠና ለማሳካትም በደብረ ማርቆስ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፤ በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና በከንቲባ ጽህፈት ቤት የግንዛቤ ፈጠራ ስራ እየተካሄደ ነው ብለዋል።


የደብረ ማርቆስ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ መምህር ባንተጊዜ ዘላለም በበኩላቸው፥ የኮደርስ ስልጠናው የወጣቱን የቴክኖሎጂ እውቀት በማሳደግ ተወዳዳሪ እንደሚያደርግ ገልፀዋል።


ያገኙትን የቴክኖሎጂ እውቀት በመጠቀም በኦንላይን ስራ የመፍጠርና ተቀጥሮ የመስራት እድልን የሚከፍት መሆኑን ተናግረዋል።


በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ዳታሳይንስ፣አንድሮይድ ዲቨሎፐርና ፕሮግራሚንግ ፋንዳሜንታል ላይ በማተኮር የሚሰጠውን ስልጠና ሁሉም ሰው ቢወስድ ለሀገር እድገት መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026