የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቶችን የቴክኖሎጂ እውቀት በማሳደግ የስራ እድል እየፈጠረ ነው

Mar 10, 2025

IDOPRESS

ደብረ ማርቆስ፤የካቲት 29/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቶችን የቴክኖሎጂ እውቀት በማሳደግ ክህሎታቸው እንዲዳብር በማድረገግ የስራ እድልን ለመፍጠር እንዳገዛቸው የደብረ ማርቆስ ከተማ ወጣቶች ገለጹ።


ወጣቶቹ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ መንግስት ባመቻቸላቸው የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በመሳተፍ ወቅቱ ከሚጠይቀው ቴክኖሎጂ ጋር በመላመድ እጃቸው ላይ ባለው ስልክ መረጃዎችን በማሰስ ለስራ እድል ፈጠራ ማዋል አስችሏል።


የከተማ አስተዳደሩ ስራና ስልጠና መምሪያ ያዘጋጀውን ስልጠናው ወስደው ከተመረቁ ወጣቶች መካከል ትልቅሰው አንሙት እንዳለችው፥ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ከቴክኖሎጂ ጋር እንድትላመድ አድርጓታል።


ስልጠናውን ከመውሰዷ በፊት እጇ ላይ ያለውን ስልክ ከመደወልና ፌስቡክ ከመጠቀም የዘለለ እውቀት እንዳልነበራት አስታውሳ አሁን ባገኘችው ስልጠና የተለያዩ ፕሮግራሞችን በመስራትና መረጃዎችን በመፈለግ ለስራ እድል ፈጠራ ለማዋል እንዳገዛት አስረድታለች።


ወጣት ገነት አበባው በበኩሏ፥ የኮደርስ ስልጠና በቴክኖሎጂ ራሷን ለማብቃትና ተጠቃሚ ለመሆን እንዳገዛት ተናግራለች።


ይህን እድል ሌሎች ወጣቶችም በመጠቀም ራሳቸውን ከቴክኖሎጂው ጋር በማስተዋወቅ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከልምዷ አካፍላለች።


የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ስራና ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አቶ መኮንን ሙሉአዳም ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ቴክኖሎጂን የታጠቀ ማህበረሰብን በመገንባት ዓለም የደረሰበት የእድገት ደረጃን ለማስተካከል እየተሰራ ነው።


በበጀት ዓመቱ ከ3 ሺህ በላይ ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ እስካሁን ከ1 ሺህ 300 በላይ ወጣቶች የእድሉ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።


የታቀደውን የኮደርስ ስልጠና ለማሳካትም በደብረ ማርቆስ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፤ በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና በከንቲባ ጽህፈት ቤት የግንዛቤ ፈጠራ ስራ እየተካሄደ ነው ብለዋል።


የደብረ ማርቆስ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ መምህር ባንተጊዜ ዘላለም በበኩላቸው፥ የኮደርስ ስልጠናው የወጣቱን የቴክኖሎጂ እውቀት በማሳደግ ተወዳዳሪ እንደሚያደርግ ገልፀዋል።


ያገኙትን የቴክኖሎጂ እውቀት በመጠቀም በኦንላይን ስራ የመፍጠርና ተቀጥሮ የመስራት እድልን የሚከፍት መሆኑን ተናግረዋል።


በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ዳታሳይንስ፣አንድሮይድ ዲቨሎፐርና ፕሮግራሚንግ ፋንዳሜንታል ላይ በማተኮር የሚሰጠውን ስልጠና ሁሉም ሰው ቢወስድ ለሀገር እድገት መሰረት የሚጥል ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026