የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የዘመኑ አርበኝነት በራስ ክህሎት ኢትዮጵያን ማነጽ ነው- ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

Mar 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 01/2017(ኢዜአ)፦ በዘመኑ አርበኝነት በራሳችን ክህሎት የበለጸገች ኢትዮጵያን ማነጽ እንደሚቻል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አዘጋጅነት "ኢትዮጵያ እያሸነፈች ትሻገራለች" በሚል መሪ ሃሳብ "ክህሎት ስለ ኢትዮጵያ" ምዕራፍ ሁለት የምክክር መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ለመድረኩ መነሻነት የተሰናዳውን የኢንዱስትሪ፣ የስራ ዕድል ፈጠራና የክህሎት ልማት ተግባራትን የሚያሳይ የፎቶ አውደ ርዕይ መርቀው ከፍተዋል።


በዚሁ ወቅት በራሳችን ክህሎት የበለጸገች ኢትዮጵያን ማነጽ እንችላለን ብለዋል።

ክህሎት ስለ ኢትዮጵያ መድረክ የቀደምት ኢትዮጵያዊያን የአርበኝነት ተጋድሎ የቅኝ አገዛዝ እሳቤን ድል በነሱበት የየካቲት ወር ማግስት መዘጋጀቱ ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸዋል።

የአሁኑ ትውልድም ቅድመ አያቶቹ ከአራቱም ማዕዘናት በዓድዋ ተራሮች ተመው ለጥቁር ህዝቦች ሁሉ የነፃነት ቀንዲል ከሆኑበት የአርበኝነት የድል ታሪክና ወኔ በመላበስ በትጋት መስራት እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል።

በዚህም በቅድመ አያቶች የነፃነት የድል ታሪክ የጸናችውን ኢትዮጵያ ክህሎት ታጥቀን በዘመኑ አርበኝነት የበለጸገች ኢትዮጵያን ማነጽ እንችላለን ብለዋል።

ሁለተኛ ምዕራፍ የመጀመሪያው ዙር "ስለኢትዮጵያ" መድረክ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቡታጅራ ከተማ ሁለተኛው ዙር ደግሞ በሐረር ከተማ መካሄዱ ይታወሳል።

ክህሎት ስለ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ምዕራፍ መድረክ ላይ በቀረበ የመነሻ ጽሁፍ ምክክር እየተደረገበት ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026