
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 01/2017(ኢዜአ)፦ በዘመኑ አርበኝነት በራሳችን ክህሎት የበለጸገች ኢትዮጵያን ማነጽ እንደሚቻል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አዘጋጅነት "ኢትዮጵያ እያሸነፈች ትሻገራለች" በሚል መሪ ሃሳብ "ክህሎት ስለ ኢትዮጵያ" ምዕራፍ ሁለት የምክክር መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ለመድረኩ መነሻነት የተሰናዳውን የኢንዱስትሪ፣ የስራ ዕድል ፈጠራና የክህሎት ልማት ተግባራትን የሚያሳይ የፎቶ አውደ ርዕይ መርቀው ከፍተዋል።

በዚሁ ወቅት በራሳችን ክህሎት የበለጸገች ኢትዮጵያን ማነጽ እንችላለን ብለዋል።
ክህሎት ስለ ኢትዮጵያ መድረክ የቀደምት ኢትዮጵያዊያን የአርበኝነት ተጋድሎ የቅኝ አገዛዝ እሳቤን ድል በነሱበት የየካቲት ወር ማግስት መዘጋጀቱ ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸዋል።
የአሁኑ ትውልድም ቅድመ አያቶቹ ከአራቱም ማዕዘናት በዓድዋ ተራሮች ተመው ለጥቁር ህዝቦች ሁሉ የነፃነት ቀንዲል ከሆኑበት የአርበኝነት የድል ታሪክና ወኔ በመላበስ በትጋት መስራት እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል።
በዚህም በቅድመ አያቶች የነፃነት የድል ታሪክ የጸናችውን ኢትዮጵያ ክህሎት ታጥቀን በዘመኑ አርበኝነት የበለጸገች ኢትዮጵያን ማነጽ እንችላለን ብለዋል።
ሁለተኛ ምዕራፍ የመጀመሪያው ዙር "ስለኢትዮጵያ" መድረክ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቡታጅራ ከተማ ሁለተኛው ዙር ደግሞ በሐረር ከተማ መካሄዱ ይታወሳል።
ክህሎት ስለ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ምዕራፍ መድረክ ላይ በቀረበ የመነሻ ጽሁፍ ምክክር እየተደረገበት ይገኛል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026