የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በሲዳማ ክልል ባለሀብቶች የሚያደርጉትን የልማት ተሳትፎ እንዲያጠናክሩ ተጠየቀ

Mar 11, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ መጋቢት 1/2017 (ኢዜአ ):-በሲዳማ ክልል ባለሀብቶች የሚያደርጉትን የልማት ተሳትፎ እንዲያጠናክሩ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ በየነ በራሳ ጠየቁ፡፡

በክልሉ ከሚገኙ ባለሀብቶች ጋር በልማትና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጓል።


አቶ በየነ በራሳ በውይይቱ ላይ እንዳሉት በክልሉ በኢኮኖሚያዊና በማህበራዊ ዘርፎች የህዝቡን መሰረታዊ ፍላጎት ለማሟላት አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው።

በዚህ ሂደትም የባለሀብቶች ተሳትፎ የላቀ መሆኑን አንስተው የክልሉ መንግስት ይህንን ተሳትፎ በማሳደግ ልማትን ለማረጋገጥ ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በሌላ በኩል ከሲዳማ ህዝብ የቆየ የመረዳዳት እሴት የመነጨ “ካእላሞ” የተሰኘ የተራድኦ ኢኒሼቲቭ በመቅረፅ ወደ ሥራ መግባቱን ገልፀው ኢኒሼቲቩ አነስተኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎችን መደገፉን አብራርተዋል፡፡

በመድረኩ ከተሳተፉ ባለሀብቶች መካከል አቶ ዘሪሁን ቃሚሶ፤ የክልሉ መንግስት ከባለሀብቱ ጋር በመተባበር የህዝቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሥራዎች እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።


ከክልሉ መንግስትጋር በኢኮኖሚ ዘርፎች፣ በትምህርት፣ በጤናና በሌሎች ማህበራዊ መስኮች በትብብር በመስራት ውጤታማ መሆናቸውን አንስተዋል።

''ከክልሉ መንግስት ጋር ያለንን ትብብር በማጠናከርም ለዜጎች የሥራ ዕድልን የሚያሰፉ ሥራዎችን እንሰራለን'' ብለዋል፡፡

በትምህርት ቤቶች ግንባታ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ህዝቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ ሥራዎች ላይ መሳተፋቸውን ያነሱት ደግሞ ሌላው ባለሀብት አቶ መስፍን ቂጤሳ ናቸው።


በመንግስትና በባለሀብቱ ተሳትፎ በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት የታየባቸው መሆኑን አስረድተው የሚያደርጉትን ተሳትፎ እንደሚያጠናክሩም ተናግረዋል፡፡

በመድረኩ ላይ የክልሉ መንግስት የስራ ሃላፊዎችና ባለሀብቶች ተሳትፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026