የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በቡኢ ከተማ አስተዳደር የችፑድ ፋብሪካ ሊገነባ ነው

Mar 12, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና፤መጋቢት 3/2017(ኢዜአ) ፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቡኢ ከተማ አስተዳደር የችፑድ ፋብሪካ ሊገነባ ነው፡፡


ለሚገነባው የችፑድ ፋብሪካም በዛሬው እለት ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የመሰረተ ድንጋይ አኑረዋል፡


በቻይናዊያን ባለሀብቶች በ5 ቢሊዮን ብር ካፒታል የሚለማው "የብሉ ኤሌፋንት ችፑድ ፋብሪካ " ግንባታው በአንድ ዓመት ጊዜ ተጠናቆ ወደማምረት ስራ እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡


ፋብሪካው ዘመኑ ባፈራቸው ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ ጥራቱን የጠበቁ የችፑድ ምርቶች በማምረት ለዓለም አቀፍ ገበያ የሚያቀርብ ሲሆን፤ ከአንድ ሺህ በላይ ዜጎች የስራ እድል እንደሚፈጥርም ተገልጿል፡፡


በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉና የምስራቅ ጉራጌ ዞን አስተዳደር የስራ ሃላፊዎች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.