የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ምርታማነታቸውን ይበልጥ ማሳደግና የክልሉን ኢኮኖሚ ማገዝ አለባቸው - ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን(ዶ/ር)

Mar 13, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር፤ መጋቢት 3/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የመንግስት የልማት ድርጅቶች አዳዲስ አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ምርታማነታቸውን ይበልጥ ማሳደግና የክልሉን ኢኮኖሚ ማገዝ እንዳለባቸው የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) ገለጹ።

የክልሉ የመንግስት የልማት ድርጅቶች የ2017 በጀት ዓመት የሰባት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ዛሬ በባህር ዳር ከተማ ተካሂዷል።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ የልማት ድርጅቶቹ አዳዲስ አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ምርታማነታቸውን ማሳደግና የክልሉን ኢኮኖሚ ማገዝ ይገባቸዋል።


የክልሉን የገቢ አቅም በማሳደግ የህዝቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ተጨማሪ ኢንቨስትመንት ላይ ትኩረት አድርገው መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።

የመንግስት የልማት ድርጅቶች ትርፋማ ለመሆንና ተጨማሪ ኢንቨስትመንቶችን በመክፈት ክልሉን በኢኮኖሚ ልማት ተወዳዳሪ ለማድረግ የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸውም ገልጸዋል።

ባለፉት ወራትም ክልሉ በችግር ውስጥ ሆኖ አብዛኞቹ የልማት ድርጅቶች ጠንክረው በመስራታቸው ትርፋማና ስኬታማ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በቀጣይም አሁን ያስመዘገቡትን ትርፍ በማሳደግ የክልሉን ልማት ይበልጥ ለማፋጠን ጠንክረው መስራት ይገባቸዋል ነው ያሉት።


የክልሉ የልማት ድርጅቶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ አበባው ጌቴ በበኩላቸው፤ በክልሉ በኮንስትራክሽን፣ በኢንዱስትሪ፣ በግብርናና በአገልግሎት ዘርፎች 12 የመንግስት የልማት ድርጅቶች እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ ብለዋል።

የልማት ድርጅቶቹ በክልሉ የነበረውን ችግር ተቋቁመው ባለፉት ሰባት ወራት ባከናወኑት ተግባር ትርፋማ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ድርጅቶቹ ከኢኮኖሚ ልማት በተጨማሪ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በትምህርትና ሌሎች ማህበራዊ ዘርፎች ላይ በመሳተፍ ሃላፊነታቸውን እየተወጡና ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል እየፈጠሩ መሆኑን ተናግረዋል።

በቀሪ ወራትም የእርስ በእርስ የልምድ ልውውጥን በማሳደግ ውጤታማ ተግባራትን እንዲያከናውኑ ይሰራል ብለዋል።

ኮርፖሬሽኑ በመስኖ ግንባታና በመጠጥ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ዘርፍ ተሰማርቶ እየሰራ እንደሚገኝ የገለጹት ደግሞ የውሃ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዘመነ ፀሐይ ናቸው።

በተለይ በመጠጥ ውሃ ዘርፍ የህብረተሰቡን የረጅም ጊዜ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠትና ተጠቃሚ ለማድረግ በተለያዩ አካባቢዎች እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ኮርፖሬሽኑ በመስኖ ግንባታና በመጠጥ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ እያከናወነ ባለው ሥራም ከ10ሺህ ለሚበልጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠሩንም አስታውቀዋል።

ለአንድ ቀን በተካሄደው የግምገማ መድረክ ላይ የክልሉ የልማት ድርጅቶች የሥራ ሃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026