የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በድሬዳዋ ለህዳሴ ግድብ ግንባታ 10 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል

Mar 13, 2025

IDOPRESS

አዲስን አበባ፤ መጋቢት 3/2017 (ኢዜአ)፦በድሬዳዋ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግንባታ 10 ሚሊዮን ለመሰበሰብ መታቀዱን የከተማ አስተዳደሩ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የህዝብ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

ገቢው የሚሰበሰበው የግድቡ ግንባታን 14ኛ ዓመት በማስመልከት መሆኑን የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አሰፋ ገልጸዋል።

ለዚህም ሰፊ የህዝብ ንቅናቄ የመፍጠር፣ የቦንድ ግዢ እና ሌሎች የገቢ ማሰባሰቢያ ስራዎች እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል።

የግድቡ ግንባታ ቀሪ ስራዎች ለማጠናቀቅ የተጀመረውን የቦንድ ግዢ ገቢ ለማሰባሰብ በአስተዳደሩ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የተለያዩ የገቢ ማስገኛ የንቅናቄ ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል።

አቶ ሀብታሙ ሁሉም ዜጋ ለግድቡ እያደረገ ያለውን ድጋፍ እና ህዝባዊ ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

መረጃው የድሬዳዋ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ነው::

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026