የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በድሬዳዋ ለህዳሴ ግድብ ግንባታ 10 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል

Mar 13, 2025

IDOPRESS

አዲስን አበባ፤ መጋቢት 3/2017 (ኢዜአ)፦በድሬዳዋ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግንባታ 10 ሚሊዮን ለመሰበሰብ መታቀዱን የከተማ አስተዳደሩ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የህዝብ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

ገቢው የሚሰበሰበው የግድቡ ግንባታን 14ኛ ዓመት በማስመልከት መሆኑን የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አሰፋ ገልጸዋል።

ለዚህም ሰፊ የህዝብ ንቅናቄ የመፍጠር፣ የቦንድ ግዢ እና ሌሎች የገቢ ማሰባሰቢያ ስራዎች እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል።

የግድቡ ግንባታ ቀሪ ስራዎች ለማጠናቀቅ የተጀመረውን የቦንድ ግዢ ገቢ ለማሰባሰብ በአስተዳደሩ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የተለያዩ የገቢ ማስገኛ የንቅናቄ ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል።

አቶ ሀብታሙ ሁሉም ዜጋ ለግድቡ እያደረገ ያለውን ድጋፍ እና ህዝባዊ ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

መረጃው የድሬዳዋ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ነው::

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.