የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የቁም እንስሳት የወጪ ገበያን ለማጠናከር ያለመ የበይነ-መረብ ውይይት ተካሄደ

Mar 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤መጋቢት 4/2017(ኢዜአ)፦የንግድ እና ቀጠናዊ ሚንስትር ካሳሁን ጎፌ ( ዶ/ር) ሰብሳቢነት የቁም እንስሳት የወጪ ንግድን አስመልክቶ በበይነ-መረም ውይይት ተደርጓል።

በውይይቱም በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት በተለይም የኮንትሮባንድ ንግድ እንዲሁም የላኪዎችን አቅም ከማጠናከር አንፃር ያሉ ውስንነቶችን ለመቅረፍ መወሰድ ያለባቸው እርምጃዎች ዙሪያ ምክክር አድርገዋል።

በቀጣይም ኢትዮጵያ ካላት ከፍተኛ የቁም እንስሳት ሀብት አንፃር በዘርፉ ተወዳዳሪ እንድትሆን ሌሎች የፌደራል ተቋማትንም በማካተት ቀጣይነት ባለው መልኩ በቅንጅት ለመስራት ተስማምተዋል።

በውይይቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ኃላፊዎች፣ የሚመለከታቸው የፌዴራል ተቋማት፣ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ-ሪያድ እና የኢትዮጵያ ቆንሳላ ጄኔራል-ጂዳ እና በጂቡቲ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ የሚሲዮን መሪዎች መሳተፋቸውን ጅቡቲ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የተገኝ መረጃ ያመለክታል።


#Ethiopian_News_Agency


#Ethiopia


#ኢዜአ

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026