
አዲስ አበባ ፤መጋቢት 4/2017(ኢዜአ)፦የንግድ እና ቀጠናዊ ሚንስትር ካሳሁን ጎፌ ( ዶ/ር) ሰብሳቢነት የቁም እንስሳት የወጪ ንግድን አስመልክቶ በበይነ-መረም ውይይት ተደርጓል።
በውይይቱም በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት በተለይም የኮንትሮባንድ ንግድ እንዲሁም የላኪዎችን አቅም ከማጠናከር አንፃር ያሉ ውስንነቶችን ለመቅረፍ መወሰድ ያለባቸው እርምጃዎች ዙሪያ ምክክር አድርገዋል።
በቀጣይም ኢትዮጵያ ካላት ከፍተኛ የቁም እንስሳት ሀብት አንፃር በዘርፉ ተወዳዳሪ እንድትሆን ሌሎች የፌደራል ተቋማትንም በማካተት ቀጣይነት ባለው መልኩ በቅንጅት ለመስራት ተስማምተዋል።
በውይይቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ኃላፊዎች፣ የሚመለከታቸው የፌዴራል ተቋማት፣ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ-ሪያድ እና የኢትዮጵያ ቆንሳላ ጄኔራል-ጂዳ እና በጂቡቲ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ የሚሲዮን መሪዎች መሳተፋቸውን ጅቡቲ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የተገኝ መረጃ ያመለክታል።
#Ethiopian_News_Agency
#Ethiopia
#ኢዜአ
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026