
አዲስ አበባ ፤መጋቢት 4/2017(ኢዜአ)፦የንግድ እና ቀጠናዊ ሚንስትር ካሳሁን ጎፌ ( ዶ/ር) ሰብሳቢነት የቁም እንስሳት የወጪ ንግድን አስመልክቶ በበይነ-መረም ውይይት ተደርጓል።
በውይይቱም በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት በተለይም የኮንትሮባንድ ንግድ እንዲሁም የላኪዎችን አቅም ከማጠናከር አንፃር ያሉ ውስንነቶችን ለመቅረፍ መወሰድ ያለባቸው እርምጃዎች ዙሪያ ምክክር አድርገዋል።
በቀጣይም ኢትዮጵያ ካላት ከፍተኛ የቁም እንስሳት ሀብት አንፃር በዘርፉ ተወዳዳሪ እንድትሆን ሌሎች የፌደራል ተቋማትንም በማካተት ቀጣይነት ባለው መልኩ በቅንጅት ለመስራት ተስማምተዋል።
በውይይቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ኃላፊዎች፣ የሚመለከታቸው የፌዴራል ተቋማት፣ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ-ሪያድ እና የኢትዮጵያ ቆንሳላ ጄኔራል-ጂዳ እና በጂቡቲ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ የሚሲዮን መሪዎች መሳተፋቸውን ጅቡቲ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የተገኝ መረጃ ያመለክታል።
#Ethiopian_News_Agency
#Ethiopia
#ኢዜአ
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026