
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 3/2017(ኢዜአ)፦ የሪል ስቴት ልማትና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅ ተግባራዊ መሆን በዘርፉ የሚከናወኑ ተግባራት ወጥነት እንዲኖራቸው አቅም እንደሚፈጥር መሆኑን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።
ሚኒስቴሩ በሪል ስቴት ልማትና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅ አተገባበር ዙሪያ ከክልል የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮዎች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄዷል።
የከተማና መሰረተ ልማት ሚንስትር ዴኤታ ሄለን ደበበ በዚህ ወቅት፤ የሪል ስቴት ልማትና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ ተገቢው ትኩረት ሳያገኙ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡
ይህን ተከትሎ በዘርፉ የሪል ስቴት ልማትና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ የማህበረሰቡን ፍላጎት ታሳቢ ሳያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡
መንግስት ከዘርፉ ማግኘት የሚገባውን ገቢ በአግባቡ እንዳይሰበስብ፣ ስራዎች በመረጃ ላይ የተመሰረቱ እንዳይሆኑ ብሎም እንደ ሀገር ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል እንዲኖር በሚሰሩ ተግባራት ላይ ማነቆ ሆኖ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡
ጠንካራ የሆነ አዋጅ ባለመኖሩ እንደ ሀገር የህብረተሰቡን የቤት አቅርቦት ጥያቄ ለመመለስ አዳጋች አድርጎት ጭምር መቆየቱን ጠቅሰዋል፡፡
የዘርፉን ችግር ለመቅረፍ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሪል ስቴት ልማትና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅ ቁጥር 1357/2017 መፅደቁን አስታውሰዋል።
አዋጁ በውጤታማ ተፈጻሚ እንዲሆን በክልል ያሉ አስፈፃሚና ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባ ሚንስትር ዴኤታዋ አሳስበዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ የመንግስት ህንፃዎችና ቤቶች ልማት አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ኢብሳ ሙሳ፤ በአዋጁ ዙሪያ ግልፅነትን ለመፍጠር እና ለአተገባበሩ ውጤታማነት ምክክር መደረጉ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

ለአዋጁ ውጤታማነት በዘርፉ የተሰማሩ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ሚና ሊጫወቱ ይገባል ያሉት ደግሞ በሀረሪ ክልል የቤቶች ልማትና የመንግስት ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ የቤት ማስተላለፍና አስተዳደር ዳይሬክተር ሙራድ አልዋን ናቸው።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026