የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

አዋጁ የሪል ስቴት ልማትና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ ተግባራት ወጥነት እንዲኖራቸው አቅም የሚፈጥር ነው

Mar 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 3/2017(ኢዜአ)፦ የሪል ስቴት ልማትና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅ ተግባራዊ መሆን በዘርፉ የሚከናወኑ ተግባራት ወጥነት እንዲኖራቸው አቅም እንደሚፈጥር መሆኑን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ በሪል ስቴት ልማትና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅ አተገባበር ዙሪያ ከክልል የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮዎች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄዷል።

የከተማና መሰረተ ልማት ሚንስትር ዴኤታ ሄለን ደበበ በዚህ ወቅት፤ የሪል ስቴት ልማትና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ ተገቢው ትኩረት ሳያገኙ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡

ይህን ተከትሎ በዘርፉ የሪል ስቴት ልማትና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ የማህበረሰቡን ፍላጎት ታሳቢ ሳያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡

መንግስት ከዘርፉ ማግኘት የሚገባውን ገቢ በአግባቡ እንዳይሰበስብ፣ ስራዎች በመረጃ ላይ የተመሰረቱ እንዳይሆኑ ብሎም እንደ ሀገር ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል እንዲኖር በሚሰሩ ተግባራት ላይ ማነቆ ሆኖ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡

ጠንካራ የሆነ አዋጅ ባለመኖሩ እንደ ሀገር የህብረተሰቡን የቤት አቅርቦት ጥያቄ ለመመለስ አዳጋች አድርጎት ጭምር መቆየቱን ጠቅሰዋል፡፡

የዘርፉን ችግር ለመቅረፍ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሪል ስቴት ልማትና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅ ቁጥር 1357/2017 መፅደቁን አስታውሰዋል።

አዋጁ በውጤታማ ተፈጻሚ እንዲሆን በክልል ያሉ አስፈፃሚና ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባ ሚንስትር ዴኤታዋ አሳስበዋል።


የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ የመንግስት ህንፃዎችና ቤቶች ልማት አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ኢብሳ ሙሳ፤ በአዋጁ ዙሪያ ግልፅነትን ለመፍጠር እና ለአተገባበሩ ውጤታማነት ምክክር መደረጉ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።


ለአዋጁ ውጤታማነት በዘርፉ የተሰማሩ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ሚና ሊጫወቱ ይገባል ያሉት ደግሞ በሀረሪ ክልል የቤቶች ልማትና የመንግስት ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ የቤት ማስተላለፍና አስተዳደር ዳይሬክተር ሙራድ አልዋን ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026