የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ባለሥልጣኑ የፓተንት ትብብር ቃልኪዳን ለመፈረም የዝገጅት ሥራዎችን እያከናወነ ነው

Mar 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን የፓተንት ትብብር ቃልኪዳን ለመፈረም የዝገጅት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ።

ባለስልጣኑ ፓተንትን በዓለም ዙሪያ በቀላሉ ማስመዝገብ የሚያስችለውን የፓተንት ትብብር ቃል ኪዳን ለማፀደቅ የግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ አካሂዷል።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወልዱ ይመስል በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ ፈጠራን የሚያበረታታ ምቹ የንግድ ከባቢ መፍጠር እና ተወዳዳሪነትን ማሳደግ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ትኩረት ከተሰጣቸው መስኮች ዋነኛው ነው።


በዘርፉ ዓለም አቀፍ ተሳትፎንና ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ ባለሥልጣኑ በህግ ማዕቀፍ፣ በአገልግሎት አሰጣጥ፣ ግንዛቤ የማሳደግ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም በጥቅምት 2017 የፓሪስ የኢንዱስትሪያዊ ንብረት ስምምነት እና የማድሪድ ዓለም አቀፍ የንግድ ምልክት ምዝገባ ፕሮቶኮል በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መፅደቁን አስታውሰዋል።

የዓለም የአእምሯዊ ንብረት ድርጅት ከሚያስተዳድራቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች መካከል ወሳኝ የሆነውን የፓተንት ትብብር ቃልኪዳን ለመፈረም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

ቃልኪዳኑ ዓለምን የሚያስተሳስር በተበታተነ ሁኔታ የሚሰጡ የፓተንት ማመልከቻ አቀራረብ ወጥ በመሆነ መንገድ ማቅረብ እንደሚያስችልም ገልፀዋል።

በአመልካቹ ፍላጎት ላይ በመመስረት ቀልጣፋ፣ ጊዜና ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ማመልከቻው እንዲመዘገቡ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡

ቃልኪዳኑን ለመፈረም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመወያየት ግብዓት የማሰባሰብ ስራ እየተሰራ መሆኑንም ጠምረው ተናግረዋል።


በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኢኖቬሽን ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ ሰላም ይሁን የፓተንት ትብብር ቃልኪዳን መፈረም የሀገር ውስጥ ስታርታፖች ቀልጣፋ፣ ጊዜና ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ማመልከቻውን እንዲያቀርቡ ያስችላል ነው ያሉት።

በውይይቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላትን ጨምሮ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026