የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የሐረር በርን ለዓለም ህዝብ የሚያስተዋውቅ በአረንጓዴ መብራት የማድመቅ ፕሮጀክት ተካሄደ

Mar 17, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ መጋቢት 7/2017(ኢዜአ)፡- የሐረር በርን ለዓለም ህዝብ የሚያስተዋውቅ በአረንጓዴ መብራት የማድመቅ ፕሮጀክት በአየርላንድ መንግስት አማካኝነት ተከናወነ።

በሥነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት በኢትዮዽያ የአየርላንድ ኤምባሲ ቆንስላ ስቴፈን ፍሬን እንደተናገሩት የአየርላንድ መንግስት ባህላዊና ታሪካዊ ቅርሶችን ለዓለም የማስተዋወቅ ስራ እያከናወነ ነው።

በአየርላንድ መንግስት የሚደገፈው ዓለም አቀፉ የአረንጓዴ መብራት ፕሮጀክት የሐረር በር በምሽት በአረንጓዴ መብራት በማድመቅ ያለውን መስህብ ለዓለም ህዝብ ማስተዋወቅ ነው።

ፕሮጀክቱ ከዚህ በፊት የላሊበላውን ቤተ ጊዮርጊስ እና የፋሲል ግንብን የመሳሰሉ ቅርሶችን እንዲሁም ሌሎች ተቋማትን በምሽት በአረንጓዴ መብራት በማድመቅ ለዓለም ህዝብ እንዲተዋወቁ አድርጓል።


ዘንድሮም የሀረር በርን በአረንጓዴ መብራት እንዲደምቅ በማድረግ የማስተዋወቅ ስራ ተከናውናል ብለዋል።

የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ አቶ እሸቱ አሰፋ ለኢዜአ እንደገለጹት የአረንጓዴ መብራትን የማድመቅ ፕሮግራም የቱሪዝም መዳረሻዎችን በዘላቂነት በማጎልበት የማስተዋቅ ተግባር ነው።

ይህም መዳረሻዎቹን ለመላው ዓለም በማስተዋወቅ ጎብኚዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ የማድረግ ዓላማ እንዳለው ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደምም በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ታሪካዊና ጥንታዊ ቅርሶችን በአረንጓዴ መብራት በማድመቅ የተከናወነው የማስተዋወቅ ስራ ቅርሶቹ በዓለም ላይ ደምቀው እንዲታዩ ማስቻሉን ተናግረዋል።

በሐረሪ ክልል ባህል ቱሪዝምና ቅርስ ቢሮ የቱሪዝም ዳይሬክተር አቶ ሳሚ አብዱልዋሲ በበኩላቸው ኤምባሲው ያከናውነው ስራ በክልሉ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎች ተደራሽነታቸው እንዲሰፋ የሚያስችል ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026