
ሐረር፤ መጋቢት 7/2017(ኢዜአ)፡- የሐረር በርን ለዓለም ህዝብ የሚያስተዋውቅ በአረንጓዴ መብራት የማድመቅ ፕሮጀክት በአየርላንድ መንግስት አማካኝነት ተከናወነ።
በሥነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት በኢትዮዽያ የአየርላንድ ኤምባሲ ቆንስላ ስቴፈን ፍሬን እንደተናገሩት የአየርላንድ መንግስት ባህላዊና ታሪካዊ ቅርሶችን ለዓለም የማስተዋወቅ ስራ እያከናወነ ነው።
በአየርላንድ መንግስት የሚደገፈው ዓለም አቀፉ የአረንጓዴ መብራት ፕሮጀክት የሐረር በር በምሽት በአረንጓዴ መብራት በማድመቅ ያለውን መስህብ ለዓለም ህዝብ ማስተዋወቅ ነው።
ፕሮጀክቱ ከዚህ በፊት የላሊበላውን ቤተ ጊዮርጊስ እና የፋሲል ግንብን የመሳሰሉ ቅርሶችን እንዲሁም ሌሎች ተቋማትን በምሽት በአረንጓዴ መብራት በማድመቅ ለዓለም ህዝብ እንዲተዋወቁ አድርጓል።

ዘንድሮም የሀረር በርን በአረንጓዴ መብራት እንዲደምቅ በማድረግ የማስተዋወቅ ስራ ተከናውናል ብለዋል።
የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ አቶ እሸቱ አሰፋ ለኢዜአ እንደገለጹት የአረንጓዴ መብራትን የማድመቅ ፕሮግራም የቱሪዝም መዳረሻዎችን በዘላቂነት በማጎልበት የማስተዋቅ ተግባር ነው።
ይህም መዳረሻዎቹን ለመላው ዓለም በማስተዋወቅ ጎብኚዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ የማድረግ ዓላማ እንዳለው ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደምም በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ታሪካዊና ጥንታዊ ቅርሶችን በአረንጓዴ መብራት በማድመቅ የተከናወነው የማስተዋወቅ ስራ ቅርሶቹ በዓለም ላይ ደምቀው እንዲታዩ ማስቻሉን ተናግረዋል።
በሐረሪ ክልል ባህል ቱሪዝምና ቅርስ ቢሮ የቱሪዝም ዳይሬክተር አቶ ሳሚ አብዱልዋሲ በበኩላቸው ኤምባሲው ያከናውነው ስራ በክልሉ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎች ተደራሽነታቸው እንዲሰፋ የሚያስችል ነው ብለዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026