
ሀዋሳ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል ለ2017/18 የምርት ዘመን ጥቅም ላይ የሚውል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ እየቀረበ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ገለፀ።
የቢሮው ምክትልና የግብርና ግብአት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ለገሰ ሀንካርሶ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ለ2017/18 የምርት ዘመን የሚሆን 300 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እየቀረበ ነው።

እስካሁንም 70 ሺህ ኩንታል ዩሪያና ዳፕ የአፈር ማዳበሪያ የበልግ እርሻ ቀድሞ በሚጀመርባቸው አካባቢዎች ለሚገኙ አርሶ አደሮች እየቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።
በሲዳማ ኤልቶ ዩኒየን በኩል በ121 ማሰራጫ ጣቢያዎች የአፈር ማዳበሪያውን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ መደረጉንም ተናግረዋል።

በበጋ መስኖ በአንድ ሄክታር መሬት ላይ ለሚያከናውኑት ልማት ማዳበሪያ ማግኘታቸውን የገለጹት ደግሞ በክልሉ የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ አርሶ አደር ገብሬ ቤሴሬ ናቸው።
የአፈር ማዳበሪያ በበቂ ሁኔታ በማግኘታቸው ለበልግ እርሻ የማሳ ዝግጅት ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።

ሌላው የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር በየነ ጣኢሮ በበኩላቸው የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ በማግኘታቸው የበልግ እርሻ ሥራ መጀመራቸውን ተናግረዋል።
በበጋ መስኖ በሁለት ሄክታር መሬት ላይ ያለሙትን ጥቅል ጎመንና ቃሪያ በማንሳት በአሁኑ ወቅት ለበልግ እርሻ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026