
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፦ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው ከኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ ፕሬዝዳንት ዲልማ ሩሴፍ ጋር ዛሬ በቻይና ሻንጋይ ከተማ ተወያይተዋል።
ውይይቱ ኢትዮጵያ የባንኩ አባል ለመሆን ያቀረበችው ጥያቄ ያለበት ደረጃ እና የሁለቱ ወገኖች የጋራ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ (በቀድሞ አጠራሩ የብሪክስ ልማት ባንክ) በብሪክስ አባል ሀገራት እ.አ.አ በ2014 ተቋቁሞ ከአንድ ዓመት በኋላ በ2015 ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል።
ግዙፉ የባለብዝሃ ወገን የልማት ባንክ ስምንት አባል ሀገራት አሉት።
ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ባንግላዴሽ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እና ግብጽ የባንኩ አባል ሀገራት ናቸው።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026